ስለ ሥላሴ የሙስሊሞች የተሳሳተ መረዳት እና እርማቱ|| He LAUGHED at the TRINITY, Until I Said. . .|| David Wood Amharic
I found this video useful, so I translated it to the best of my ability. Use this link to find the first video I translated from. I apologize for the minor mistakes I make.
• He LAUGHED at the TRIN...
መልካም ዜና
የምስራች፣ የምስራች፣ የምስራች! የምስራች ማለት መልካም ዜና ማለት ነው። የእግዚአብሔር ቃል ደጋግሞ የሚነግረን ይሄ መልካም ዜና ምንድነው? ዛሬ፣ በእግዚአብሔር ረዳትነት፣ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለተጠቀሰው ስለዚህ መልካም ዜና እንነጋገራለን። ነገር ግን ስለ መልካሙ ዜና ከመነጋገራች በፊት ስለ መጥፎው ዜና ማስታወስ አለብን።
ምንድነው መጥፎው ዜና? በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ በኋላ አዳምንና ሔዋንን በምድራዊዋ ገነት ውስጥ እንዳስቀመጣቸው ታስታውሳላችሁ። እግዚአብሄር እንዲያውቁት፣ እንዲወዱት፣ እንዲታዘዙት እና ለዘላለም እንዲያከብሩት ፈጥሯቸዋል። ይሁን እንጂ እግዚአብሔር እነሱን ለመፈተን አዳምን እንዲህ አለው፡-
“በገነት ካለው ከዛፉ ፍሬ ብሉ፥ ነገር ግን እንዳትሞቱ በገነት መካከል ካለው ከዛፉ ፍሬ አትብሉ አትንኩትም።”
መጥፎው ዜና አዳምና ሔዋን እባቡን ማለትም ከተከለከለው ዛፍ ፍሬ እንዲበሉ የፈተናቸውን ዲያብሎስን ማዳመጣቸው ነው። የአዳምና የሔዋን ኃጢአት እነርሱንና ዘሮቻቸውን ሁሉ በመበከል በዓለም ላይ ችግርንና ሞትን አመጣ። ብዙ ጊዜ እንደምንሰማው፡ "ወረርሽኝ መነሻው ላይ ብቻ አይወሰንም!" የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጥፎ ዜና ይነግረናል፡-
“ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥...
እነሆ፥ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ፥ በኃጢአተኝነትም ስላደረጉት ስለ ኃጢአተኛ ሥራቸው ሁሉ ዓመፀኞችም ኃጢአተኞች በእርሱ ላይ ስለ ተናገሩ ስለ ጭከና ነገር ሁሉ ኃጢአተኞችን ሁሉ እንዲወቅስ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ።” (ዕብራውያን 9፥27 ይሁዳ 1፥15)
ስለዚህ፣ መጥፎው ዜና ሁላችንም ኃጢአተኞች ነን እናም የእግዚአብሔርን የጽድቅ ፍርድ መጋፈጥ አለብን! ይሁን እንጂ፣ መልካሙ ዜና (የምስራቹ) በዚያው በገነት ውስጥ፣ በምረቱ ባለጠጋ የሆነው እግዚአብሔር፣ አንድ ቀን ከድንግል የሚወለድን ኃጢአት የሌለበትን ሰው ወደ አለም እንደሚልክ ማስታወቁ ነው። ይህ ቅዱስ ሰው፣ ይህ ጻድቅ አዳኝ፣ ለአዳምና ለዘሮቹ ሁሉ ኃጢአት ለመክፈል ራሱን መስዋእት አድርጎ ይሞት ነበር። ለኛ የሚገባን የኃጢአት ቅጣት በዚህ ኃጢአት በሌለበት አዳኝ ላይ ይወድቃል። አዳምና ሔዋን ኃጢአት በሠሩበት ቀን እግዚአብሔር የሰበከው ወንጌል (የምስራች) ይህ ነው። እግዚአብሔር የዚህን አዳኝ መምጣት ለማወጅ ብዙ ሰዎችን ተጠቅሟል፣ እንዲሁም መሲህ ይባላል። እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ መሲሑ አንድ ነገር አውጀዋል፣ ስለዚህም እርሱ ሲመጣ እግዚአብሔር የሾመው እርሱ መሆኑን ሁሉም ይገነዘባል። ለምሳሌ ያህል፣ ከመሲሑ መምጣት ሰባት መቶ ዓመታት ቀደም ብሎ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስ፣ መሲሑ እንዴት እንደሚወለድ ተንብዮአል። "ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።"( ማቴ. 1:23፤ ኢሳ. 7:14 ) ሚክያስ የተባለ ነቢይ ደግሞ መሲሁ ከሰማይ መጥቶ በቤተልሄም መንደር በምድር ላይ እንደሚወለድ ትንቢት ተናግሯል። በትክክል መሲሑ የተወለደበት ቦታ ይህ ነበር። ሆኖም ሚክያስ ይህን ትንቢት የተናገረው መሲሑ ከመወለዱ ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት ነው። ነገር ግን ነቢያት የመሲሑን መወለድ ብቻ አላወጁም። በተጨማሪም መሲሁ በኃጢአተኞች ምትክ መከራ እንደሚደርስበትና እንደሚምት ትንቢት ተናግረዋል። ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ሰዎች መሲሑን እንደሚንቁት፣ እንደሚያሰቃዩት፣ እጁንና እግሩን እንደሚወጉ እና እንደሚገድሉት ጽፏል። ዳዊት የመሲሑን ሞት ማወጅ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር መሲሁን ከሞት እንደሚያስነሳውም ተንብዮአል፤ ይህም እግዚአብሔር የአዳምን ልጆች ከኃጢአት ቅጣት ለማዳን የላከው አንድና ብቸኛ አዳኝ መሆኑን አረጋግጣል።
ስለ መሲሁ መወለድ ብዙም ክርክር የለም፣ ነገር ግን ብዙዎች በሞቱና በትንሳኤው ይሰናከላሉ። ሰዎች የላከውን መሲህ ሲያዋርዱት እግዚአብሔር እንዴት ሊቆም እና ሊመለከት እንደሚችል አይገባቸውም። ብዙ ሰዎች ሊረዱት ያልቻሉት ነገር መሲሑ ለኃጢአታችን እንዲህ አይነት መከራ እንዲደርስበት ያቀደው እኛን የሚወደን አምላክ መሆኑን ነው። ነገር ግን ነቢያቱ እንዲህ ሲሉ አውጀዋል፡- “እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።”
- (ኢሳይያስ 53፥10)
ነቢያትን እናምናለን? አዎ እናምናቸዋለን እንላለን። ነቢያትን በእርግጥ የምናምን ከሆነ የጻፉትንም ማመን አለብን። ነብያት የራሳቸውን ሃሳብ እንዳልተናገሩ ማስታወስ አለብን። እግዚአብሔር የሚናገሩትን በመንፈሳቸው ውስጥ አኖረ። እንግዲያውስ እነዚያን ነቢያት ለማመን ብንቃወም፣ ማንን ነው ምንቃወመው? የምንቃወመው እግዚአብሔርን ነው። ምክንያቱም ነቢያት መሲሁ ኃጢአትን ለማስወገድ መስዋዕት ሆኖ እንደሚሞት ትንቢት እንዲተነብዩ ያነሳሳው እርሱ ነውና።
{የሚቀጥለው ማሊክ የሚባል ሰው የግል ምስክርነት ነው።} እዚህ ጋር ቆም ላድርገውና እንዴት በኢየሱስ ክርስቶስ አማኝ እንደሆንኩ ልንገራችሁ። በወጣትነቴ በቀን አምስት ጊዜ ለመጸለይ እና አመታዊ ጾምን ለመጾም ታማኝ ነበርኩ፣ ነገር ግን ከሞትኩ በኋላ ወዴት እንደምሄድ አላውቅም ነበር። ዙሪያዬ ያሉትን ሁሉ ጠየኩ፣ ሆኖም ግልጽ የሆነ መልስ አላገኘሁም። ወንጌልን (ኢንጂልን) ሳጠና ግን፣ ከሞቴ በኋላ ወዴት እንደምሄድ ማወቅ እንደምችል አወቅሁ፤ ምክንያቱም መሲሁ ኢየሱስ ራሱ በወንጌል እንዲህ ይላል፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” (ዮሐንስ 5፥24) እንዲሁም እንዲህ ብሏል፦ “ኢየሱስም፦ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤” (ዮሐንስ 11፥25) ስለዚ፣ ራሴን ለማዳን ከራሴ ጥረት ንስሃ ገብቼ ነቢያት ሁሉ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት ይቀበላል" ብለው ትንቢት በተናገሩለት መሲህ አመንኩኝ (ሐዋርያት 10፥43)። ተስፋዬን ሁሉ ወስጄ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ አስቀመጥኩት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሔር ለመንፈሴ ሰላም አምጥቶላታል። አሁን ህሊናዬ አይረበሽም። ኢየሱስ በመስቀል ላይ ከሰራው ሥራ የተነሳ የወደፊት እጣዬ በሚያስደንቅ ሁኔታ ብሩህ ነው። በሕይወቴ እንደ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር፣ አንዳንድ ጊዜ ችግር እና መከራ ያጋጥመኛል ምክንያቱም እምነቴ ከዘመዶቼ እና ከጓደኞቼ አስተያየት ስለሚለያይ፤ ግን ሰላም አለኝ። የእግዚአብሔር ሰላም ልቤንና አእምሮዬን ሞልቶታል። ይህን የሰጠኝ ኢየሱስም እንዲህ ይላል፦ “ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ።” (ዮሐንስ 15፥18) “ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።” (ዮሐንስ 14፥27) እና ወዳጆች ሆይ፣ ጌታ ለእኔ እና በእኔ ያደረገውን ለእያንዳንዳችሁ ሊያደርግ ይችላል። ካንተ ወይም ካንቺ አንድ ነገር ይጠይቃል፡-ሙሉ ልብህን እንድትሰጠው። ሙሉ ልብሽን እንድትሰጪው። የቀረውን እሱ ያደርገዋል። ጌታ ኢየሱስ ራሱ እንዲህ ብሏልና። "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤" (ማቴ. 11:28-29)
እግዚአብሔር ታላቁን ማዳኑን መቼም ቢሆን አይሸጥልህም ወይም አይሸጥልሽም። እንዲሁ ያለ ምንም ዋጋ (ከእናንተ ባልሆነ ዋጋ) በነጻ ሊሰጣችሁ ነው ሚፈልገው። መልካም ስራ፣ ፀሎት (ሶላት) እና ፆም በውስጣችሁ ጥሩ ስሜት ይሰጡ ይሆናል፣ ነገር ግን የእግዚአብሔርን ፅድቅ አያረኩም! ወደ እግዚአብሔር ገነት የምትገባበት/የምትገቢበት መንገድ አንድ ብቻ ነው።
1.) በመጀመሪያ ኃጢአተኛ እንደሆንክና አምላክን ለማስደሰት የሚያስችል ኃይል እንደሌለህ መገንዘብ ይኖርብሃል።
2.) ከዚያም ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ እንደሆነ፣ ኃጢአትህን ለማስወገድ እግዚአብሔር በመስቀል ላይ እንዲሞት እንደ ላከውና እግዚአብሔር የዘለአለም ሕይወትን ይሰጥህ ዘንድ እንዳስነሳው ማመን አለብህ።
የኦሮምኛውን ቻናሌን ለማግኘት ይህንን ተጫኑ👇
/ @dhugaanniboqachiisa
አስተያየታችሁን በውስጥ ማድረስ የምትፈልጉ ይህንን የቴሌግራም ሊንክ ተጠቀሙ👇
t.me/BibleAndMe
Additional: - ewnetyasarfal123@gmail.com
Пікірлер: 96
🔴✍️አገልግሎቴን በገንዘባችሁ መደገፍ የምትችሉ ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ አናግሩኝ። ትንሽ እገዛችሁ ያስፈልገኛል።🥰🥰🥰🥰🥰 t.me/BibleAndMe
ሙስሊሞች በደንብ ስሙ እባካችሁ ከዘላለም ሞት ታመልጡ ዘንድ ።ተባረክ ወንድማችን ወንጌላችን ገና ድል ያደርጋል 🎉🎉🎉
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን! አመሰግናለው🙏🥰
@mahammedsanishafi4277
2 ай бұрын
ለራሳችሁ በደንብ ያልገባችሁ በኮንፈራንስ የታወጀን ጉዳይ ለሙስሊም ለማስረዳት መሞከር ትርፉ ራስን መሸንገል አይሆንም? ሁሉም ባይሆንም ሙስሊሙ ከእናንተ በተሻለ ስለክሪስትናም የራሱንም እመነት አብጠርጥሮያውቃል። እግዚያቤር ቃል ነበር ቃልም እግዚያብሔር ዘንድ ነበር የምለው ላይ የሚነሳውን ጥያቄ አንዳችሁም መመለስ አልቻላችሁም። እስቲ መልሳችሁ መላልሳችሁ በሉትና ፍቱት።
@user-il7xd5qd2j
2 ай бұрын
ማድመጥማ አደመጥነው ግን ምን ዋጋ አለው መልስ ነው ብላቹ ያመጣቹት የማይገናኝ ሆኖ አስተዛዘበን እንጂ፡፡ ለስላሴ ማብራሪያ መቼም ከባይብል አታመጡም ም/ቱም ስላሴን ባይብል አያውቀውም፡፡፡ ወገን መዳን የሚቻለው አንተን እና እየሱስን የፈጠረውን አንድ አላህን በማምለክ ነው ለዛም ነው እየሱስ የአላህ ሰላምና እዝነት በሱና በእናቱ ላይ ይሁን እና በዮሐንስ ወንጌል 17:3 ላይ አብ ብቸኛ አምላክ እና እየሱስ መልክተኛ መሆኑን ገልፆዋል፡፡ እንዲሁ በዮሐንስ 20:17 ላይ በግልፅ አምላክ አለኝ እያለ አስተምሮዋል፡፡፡፡፡ እየሱስን ተከተለው ከቤተክርስቲያን አስተምህሮት ውጡ፡፡
እግዚአብሔር ይባርካችሁ ወገኖች በርቱ ወንጌላችን ገና ድል ያደርጋል
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን። አመሰግናለው🙏
@user-yt5gp3bq6x
2 ай бұрын
❤❤❤
የእግዚአብሔር ልጅ እየሱስ ክርስቶስ ስምህ ለዘላለም ይባረክ
እግዚአብሔር ይባርክህ ከዚህ በበለጠ ጌታ ያስፋህ ..መከናወንን ይስጥህ !!!!!🙌🙌🙌😍😍😍😍
እግዚሀብሔር የዘላለም አምላክ ነው ስሙ ይክበር❤❤❤
እግዚኣብሄር ይባርክህ እንዲሁም ወንድማችንንም!!
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን። አመሰግናለው🙏
በጣም የሚያሳዝነዉ ነገር ሰዉ በህይወቱ እያለ ፈጣሪዉን ክርስቶስን ከድቶ በዚህ አለም በተሰናበተ ጊዜ በዛ በአስደንጋጭ በሲኦል መባከን እንደሆነ አንዘንጋ። አቤቱ የቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ሆይ ፥ እኔ በፊትህ እንደ ትቢያ የተናኩኝ ባርያህን ዳግም ለንስሃ ሞት አብቃኝ። በኔ የሚያምንብኝ የዘላለም ህይዎትን እሰጠዋለሁ ብሎ አስገንዝቦናል። አሜን አምላኬ ፈጣሪየ እየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ በፈቀድከዉ እንሄድ ዘንድ አንተዉ እርዳን አሜን
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉እያ ተባረክ❤❤❤❤❤🙏🏼🙏🏼🙏🏼
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን። አመሰግናለው🙏
እንደ እግዝአብሔር ያለ ማንም የለም
እግብሔር ይባርክህ ።ትክክል አባባል ነው ያለከው የሌላ ሰው ወይ እምነት በመተቸት ያንተን እውነት ማድረግ አትችልም። ክርስቶስ ኢየሱስ ፍቅር ነው ትሁት ነው ፊሊጲ2:6-10
I am muslim Alhamdulillah ❤....muslim is the truth pathway
@Netflix-series33
2 ай бұрын
Muslim is false
1+1+1=1 አምላክ ያህዌ 🙏❤ ፀጋ ይብዛላችሁ
በርታ ወንድም ጌታ ከእናንተ ጋር ነው ተባረኩ 🙏🙏🙏❤️❤️
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን! አመሰግናለው🙏
I am muslim Alhamdulillah
በርቱ ወንድሞቼ ወንግል ያሸንፋል
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን። አመሰግናለው🙏
ሰዎች እዉነት እዉነት ከፈለጋቹ ሱብሀንአላህ ስንት ተአምር አለ አላህ ብዙ ታአምራት አርጓል በኢስላም ብዙ ምልክቶችን አድርጓል ሱብሀንአላህ የነብዪ ሙሀመድ ሰዐወ ታሪካቸዉን ብቻ እንኳን ብናይ እዉነተኝነታቸዉን ያለጥርጥር ሚያረጋግጥልን ነዉ. ታአማኒነቱ በተመለከተ ደግሞ ታላላቅ ምዕራባዊያን ምሁራኖች የታሪክ ተመራማሩዎች ሳያቀር እንደ ሙሀመድ ታሪክ ግልፅ ያለ የማንም የለም ሲሉ ይናገራሉ ይሄ በራሱ ታአምር ነዉ ብታስተነትኑት
በርታ ብሮየ ፈጣሪ ጸጋዉ ያብዛልህ 🙏🙏🙏
Good job
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አመሰግናለው🙏
❤ብሩክ ነህ ወንድሜ ፀጋ ይብዛልህ !
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን! አመሰግናለው🙏
Likd adregu enji
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አመሰግናለው🙏🥰🥰🥰
ስላሴ (አብ + ወልድ + መንፈስ ቅዱስ) አንድ አምላክ የሚል ከመፅሃፍ ቅዱስ መረጃ አምጡ።
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
ማስረጃዎችን በዚህ ቪድዮ ውስጥ ታገኛቸዋለህ፣ ሊንኩን ንካውና ግባ። kzread.info/dash/bejne/n6GXmJeDhcqshtI.html
@negamekonnen8056
2 ай бұрын
በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እያጠመቃችሁ ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው የሚለውን ታውቀዋለህ!?
be blessed bro!God bless you more&more🙏💝❤❤❤🎉
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አሜን! አመሰግናለው🙏
❤❤❤❤❤❤❤❤🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
ሎጂክ እና የተሳሳተ ትርጓሜ እስልምናን አላህ ስለሰጠኝ አልሀምዲሊላህ
@user-fj6zs3tz3f
2 ай бұрын
በጣም የሚያሳዝነዉ ነገር ሰዉ በህይወቱ እያለ ፈጣሪዉን ክርስቶስ ከድቶ በዚህ አለም በተሰናበተ ጊዜ በዛ በአስደንጋጭ በሲኦል መባከን እንደሆነ አትዘንጋ። አቤቱ የቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ሆይ ፥ እኔ በፊትህ እንደ ትቢያ የተናኩኝ ባርያህን ዳግም ለንስሃ ሞት አብቃኝ አሜን። መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በመጽሃፉ እንዲህ ብሎ ጽፎልናል .. በኔ የሚያምንብኝ የዘላለም ህይዎትን እሰጠዋለሁ ብሎ አስገንዝቦናል። አሜን አምላኬ ፈጣሪየ እየሱስ ክርስቶስ ሆይ አንተ በፈቀድከዉ እሄድ ዘንድ አንተዉ እርዳኝ አሜን
🙏🙏🙏
Alhamdulilah ❤❤😂muslim laregeng fetariye allah halikesemawati wel ard❤
በ VPN በማየት እተባበርሃለው🥰
Eselemena ye wushat hayemanot nawu 💯
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አመሰግናለው🙏
እኔ የሚያሳዝነኝ ኮ እዚ ምድራዊ ያለመ ነገር ለኛ እንደዙሙት የሚታየዉ ሙስሊሞች ደሞ በገነት እናደርግዋለን ብሎ እየጠበቁት ያሉ የዙሙት ገነት ነዉ ያላቸዉ😒
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
መሐመድ ከክርስትና ለመቃረን ብሎ ሁሉንም ተቃራኒ አድርጎታል።
@user-wd3ig3no4f
2 ай бұрын
ትክክል ነው
እያ እባካችሁ ይህንን የመጻፍ ቅዱስ ክፍል ለሙስልሞች ጥያቄ ማብራርያ በቪድዮ አስደግፋቹ ብታቀርብ? ማቴ 20፥20
እውቀት ካላቹ እና መልስ ከባይብል ካለ እጠብቃለሁ ከዘፍጥረት እስከ ዮሐንስ ራዕይ ባለው እንደፈለጋቹ፡፡፡ሰበካ እኔ የቤተክርስቲያን አስተምህሮት አልፈልግም፡፡፡
በመጀመሪያ ለሰው ክብር ይኑርህ ። ሲቀጥል አንተ ዝቅ አደረከው ከፍ አደረግከው ለእሱ ያንተ ከፍ ማድረግ እና ዝቅ ማድረግ ከንቱ ነት ነው ። መንገዱን እስካልተከተልክ ። ለማንኛውም ምላስህን ለከት አድርግለት ። ሲቀጥል የተጠየቅከው ሌላ የምትመልሰው ሌላ ። እንዳው የሚከተሉኝ በጎች ይታዘቡኛል አትልም ።25 ዲቃ ተረተረት ከምታወራ 5 ደቂቃ በቂ መልስ አትመልስም ።
ለምን በሂሳብ ስሌት እንደ ሚያሰሉ አላውቅም ለምን አንድ ሲባዛ አንድ ለምን አንድ ሆነ ብለዉ አይጠይቁም።
@user-il7xd5qd2j
2 ай бұрын
ወገን የማባዛት እና የመደመር ልዩነት አታውቅም???
የቃሉት ትርጉም ቃሉ የመጣው ‹‹ትሪንትስ›› ከሚል የግሪክኛ ቃል ሲሆን ‹‹የሶስት አካላት ጥምረት›› የሚል ትርጉም አለው። ‹‹ሥላሴ›› የሚለው የግዕዝ ቃልም ‹‹ሶስትነት›› የሚል ተመሳሳይ ፍች ሲኖረው አብያተክርስቲያናት የአምላክን በአካል ‹‹ሶስት›› በመለኮት ‹‹አንድ›› መሆን ለመግለፅ የሚጠቀሙበት ቃል ነው። ‹‹ሥላሴ›› የክርስትና እምነት መሰረት እንደሆነው ሁሉ ሌሎቹም ኃይማኖቶች እንዲሁ የየራሳቸው የሆነ የእምነት መሰረት አላቸው። ለአብነትም የአይሁድ የእምነት መሰረት ‹‹ሼማ›› በመባል የሚጠራ ሲሆን ቃሉ ‹‹አንድ አምላክ በአንድ አካል›› የሚል ፍች አለው። የኢስላም መሰረት ደግሞ ‹‹ተውሂድ›› በሚል ቃል ሲጠራ ትርጓሜውም ‹‹አምላክ በአካል፣ በቁጥር፣ በብዛት አንድ መለኮት ነው።›› የሚል ነው። በዓለም ላይ በአንድ አምላክ ብቻ የሚያምኑ ‹‹Monotheism›› በሚለው የእንግሊዘኛ ቃል ሲጠሩ እነሱም በዋናነት ኢስላምና አይሁድ ናቸው። ክርስትና በአምላክ ‹‹ሶስትነት›› የሚያምን በመሆኑ ‹‹Modalism›› ወይም ‹‹አንድ አምላክ በሶስት አካላት›› በሚል ቃል ይጠራል። በሶስት ፍፁማዊ አካላት አምላክነት ላይ የተመሰረተውን የሥላሴ አምላክነት የእምነቱ ምሁራን በሶስት የባህርይ ስም ይከፍሉታል። • 1ኛ፡- አብ - አባት ሲሆን አባትነቱ የባህርይ ነው። • 2ኛ፡- ወልድ - ተወላዲ ሲሆን ወልድነቱ የባህርይ ነው። • 3ኛ፡- መንፈስቅዱስ - ሰራፂ ሲሆን ሰራፂነቱ የባህርይ ነው። ሶስቱም ፍፁማዊ አምላኮች ሲሆኑ የየራሳቸው መለኮታዊ አካልና ስልጣን እንዳላቸው ይታመናል። እንዲሁም አንዱ ከአንዱ አይበልጥም፥ አንዱም ከአንዱ አይነጠልም፤ የሚል አስተምህሮት አለው። ርዕሱን በቀጣዮቹ ንዑስ ክፍሎች አንድ በአንድ እየተነተንን የምናየው ሲሆን ነገሩን ይበልጥ ለመረዳት ግን ከእምነቱ ታሪካዊ አመጣጥ እንጀምር ዘንድ ወደድኩ።ለመሆኑ የሥላሴ አስተምህሮት ታሪካዊ አመጣጥ ምን ይመስላል? ታሪካዊ ዳራው የሚነግረን እውነታ ምንድነው? ቀጣዩ ርዕስ ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጠናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።
@user-pq7si2gw7c
2 ай бұрын
ውሸታም።ሥላሴን አለማወቅህን ያሳያል።christina monotheisim ነው።አሃዱ አምላክን ያምናል
@kidist5941
Ай бұрын
@@user-pq7si2gw7cአሐዱ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጓሜውም አንድ ማለት ነው
ታሪካዊው ሥላሴ ሥላሴ በታሪካዊ ሂደት ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና እየተለወጠ የመጣ አስተምህሮት እንጅ በአንድ ጊዜ አሁን የያዘውን ቅርፅና ይዘት እንዳልያዘ የታሪክ መዛግብት ያስረዱናል። ከክርስትና መምጣት በፊት ያሉትን የነቢያት አስተምህሮቶችና በታሪክ የተመዘገቡትን የቀደምት ፃድቃን ሰዎች እምነት በምናጠናበት ወቅትም የአምላክን ሶስትነት አንዳቸውም ሰብከው እንደማያውቁ እንረዳለን። ይህም ሥላሴ የኢየሱስን መምጣት ተከትሎ የተነሳ እሳቤ እንጅ ቀድሞም የነበረ የነቢያት መንገድ እንዳልሆነ ማሳያ ነው። ለዚህም ይመስላል የቤተክርስቲያን አስተማሪዎች ስለሥላሴ ሲናገሩ ከመጽሐፍ ቅዱስ አንቀፆች ይልቅ የቀደምት አባቶች ድንጋጌ ላይ ትኩረት የሚያደርጉት። ‹‹ሥላሴ›› የሚለው ቃል ወይም ‹‹አንድ አምላክ በሶስት አካላት›› የሚለው ትንተና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በቀጥታ የተገለፀ እንዳልሆነ ሁሉም የክርስትና ምሁራን ይስማሙበታል። ‹‹ሥላሴ›› በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንድም ቦታ ያልተጠቀሰ ባዕድ ቃል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ስያሜው የተሰጠው ከመጽሐፉ የተለያዩ ጥቅሶች በመነሳት እንደሆነም ይነገራል። እርግጥ በመጠኑ በጣም ትልቅ እና የመጽሐፍት ስብስብበ ሆነው መጽሐፍ ውስጥ ቃሉ አንድም ጊዜ እንኳን አለመጠቀሱ አለባብሰን የምናልፈው ነገር አይደለም። በአስገራሚ ሁኔታ ግን ይህ ቃል ‹‹በቁርኣን›› ውስጥ ብቻ ተፅፎ እናገኘዋለን። የማዒዳህ ምዕራፍ አንቀፅ 73 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹እነዚያ አላህ የሶስት ሶስተኛ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ።›› ለመሆኑ የቃሉ መነሻ ከየት መጣ? የአስተምህሮቱ አጀማመር ምን ይመስል ነበር? የሚለውን ስናጠና መጀመሪያ ስሙ የሚጠቀሰው ቴዎፍሎስ የአንፆኪያው (170 ዓ.ል) ነው። ይህ ሰው በአሁኗ ቱርክ በምትገኘው ጥንታዊቷ የአንፆኪያ ከተማ ጳጳስ ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ሥላሴ ፍንጭ ሰጪ ሃሳቦችን የፃፈ ነው ተብሎም ይታመናል። ኢየሱስ ወደ አባቱ ካረገበት ጊዜ ጀምሮና ይህ ሰው እስከነበረበት ድረስ ባሉት 140 ዓመታት ውስጥ ስለ ሥላሴ የሚገልፅ ምንም ፅሁፍ አልተገኘም። የአንፆኪያው ጳጳስ ከሥላሴ አስተምህሮት ጋር ይቀራረባል የሚባልለት ፅሁፉ እንዲህ የሚል ነው፡- ‹‹ፀሐይ ከመፈጠሯ በፊት ያሉት ሶስት ቀናት የሥላሴ ምሳሌዎች ናቸው። የአምላክን፤ የቃሉን እና የጥበቡን። አራተኛው ቀን የሰው ምሳሌ ነው፤ ብርሃን ይፈልጋል። ስለዚህ አምላክ አለ፣ ቃሉም አለ፣ ጥበቡም አለ፣ እንዲሁም ሰው አለ።›› (1) ከዚህ ፅሁፍ የምንረዳው እግዚአብሔር ፀሐይን ከመፍጠሩ በፊት ያሉት ሶስት ቀናት ‹‹የፈጣሪ፣ የቃሉ እና የጥበቡ›› ምሳሌዎች መሆናቸውን ከመናገሩ በስተቀር የአብ የወልድና የመንፈስ ቅዱስ አምላክነትን በትክክል እንደማይገልፅ ወይም አስተምህሮቱን እንዳልደረሰበት ነው። ቴርቱሊያን (160-225 ዓ.ል) የተባለው የኃይማኖት አበው ሁለተኛው ተጠቃሽ ሰው ሲሆን ከቴዎፍሎስ ቀጥሎ ለመጀመሪያ ጊዜ በላቲነኛ ‹‹trinitas›› ወይም ‹‹ሥላሴ›› የሚለውን ቃል የፃፈ ነው። ‹‹ሥላሴ››፣ ‹‹አካል›› እና ‹‹ባህርይ›› የሚሉትን ቃላት ለያይቶ ከመፃፉም በተጨማሪ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ‹‹በባህርይ አንድ በአካል ሶስት ናቸው።›› ሲል አትቷል። ይሁን እንጅ የእሱም አስተምህሮት በሥላሴ ላይ ባለው የባህርይ ልዩነት ከዛሬው አስተምህሮት ጋር የተዛመደ አልነበረም።(2) ሌላው ስመጥር ሰው አግናጥዮስ የአንፆኪያው (35-107 ዓ.ል) ነው። ይህ ሰው የሥላሴን ትምህርት በክርስትናው ዓለም ሰብኳል የሚባልለት ሲሆን በዚህም አስተምህሮቱ ከፍተኛ እውቅናና ዝናን አግኝቷል። አግናጥዮስ በቀደምት አባቶች ዘንድ የሚታወቀውና በተለይ በሶስቱ ሥላሴዎች መካከል ስላለው አንድነትና ልዩነት የፃፈው እንዲህ የሚል ነው፡- ‹‹አብ አብ ነው እንጅ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አይደለም፤ ወልድም ወልድ ነው እንጅ አብን መንፈስ ቅዱስን አይደለም፤ መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነው እንጅ አብን ወልድን አይደለም።›› (3) ከዚህ ሁሉ ሂደት በኋላ የሥላሴን አስተምህሮት አንድ ወጥ ድንጋጌ ይዞ እንዲንቀሳቀስ ያደረገው ደግሞ አትናቴዎስ የእስክንድርያው (296-373 ዓ.ል) ነው። አትናቴዎስ በሥላሴ አስተምህሮት ላይ ትልቁን ለውጥና መሻሻል ያመጣው ሃያኛው የእስክንድርያ ጳጳስ ስለመሆኑ ሁሉም የታሪክ ምሁራን ይስማሙበታል። የዓለም አብያተክርስቲያናት ወደውም ይሁን በጫና ሥላሴን የክርስትናቸው መሰረት እንዲያደርጉት ትልቅ የፖለቲካ ጨዋታ የተጫወተ ሰው እንደሆነ ይነገራል። በአሁኑ ሰዓት ያለው የሥላሴ አስተምህሮት ሙሉ በሙሉ የአትናቴዎስ ነው ቢባልም የሚታበል አይደለም። አትናቴዎስ በሥላሴ አስተምህሮት ላይ ሁለት ዓበይት ለውጦችን አምጥቷል። አንደኛው ቀድሞ በእነ ቴዎፍሎስ፣ ቴርቱሊያን እና አግናጥዮስ እያደገ የመጣውን የሥላሴ ትምህርትለውጥና መሻሻል በማድረግ አንድ ወጥ ድንጋጌ እንዲኖረው አድርጓል። ሁለተኛው ደግሞ የመንፈስ ቅዱስን ፍፁማዊ አምላክነት ማፅደቁ ነው። ቀደምት አባቶች በመንፈስ ቅዱስ ምንነት ጉዳይ ላይ ሲወዛገቡና የተለያየ ትርጉም ሲሰጡት ቆይተዋል። ይህንን ክፍፍል ለማስወገድ አትናቴዎስ በእድሜው መገባደጃ አካባቢ ‹‹መንፈስ ቅዱስ አካል ያለው አምላክ ነው።›› ሲል ብይን ሰጥቷል። በዚህም መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ እኩል ፍፁማዊ አምላክ ተብሎ እንዲታመን ለየአብያተክርስቲያናቱ ውሳኔውን አስተላልፏል።(4) ከአትናቴዎስ የሥላሴ አስተምህሮት ድንጋጌዎች ለአብነት የመረጥኳቸው አንቀፆች እንዲህ የሚሉ ናቸው፡- ‹‹ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን። ያልተወለደ እግዚአብሔር አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው። የተወለደ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው። በወደደው የሚያድር የአብ የወልድ እስትንፋስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ አንድ ነው። አብ አልተወለደም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ወልድን የወለደ ነው እንጂ። ወልድም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ከእግዚአብሔር አብ ተወለደ። መንፈስ ቅዱስም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ከእግዚአብሔር አብ ሠረጸ።›› (5) ‹‹አብ በአካሉ በገፁ በመልኩ ያለ ነውና፤ ወልድም እንዲሁ በአካሉ በገፁ በመልኩ ያለ ነውና፤ መንፈስ ቅዱስም እንዲሁ በአካሉ በገፁ በመልኩ ያለ ነውና። እንደ ሰውም አይወሰኑም፤ አምላክነት ያለው አካላት ናቸው። በአካል ሶስት በባህርይ አንድ ብሎ ይህን ኃይማኖት የማያምን እንዲህ እኛ እንደወሰንነው አድርጎ ሃይማኖቱን የማይፅፍ ቢኖር ሃዋርያት ያስተማሯት ቅድስት ቤተክርስቲያን ታወግዛለች።›› ______________ (1) Early Christian Writingde: Theophilus of Antioch”, II.XV (2) Justo L. Gonzalez (2010). “The Story of Christianity, Vol. 1: The Early Church to the Dawn of the Reformation”, pp.91-93 (3) ሃይማኖተ አበው ዘአግንጥዮስ፡ ገፅ 37 - ክ፡1 ቁ፡8 (4) Trinity Britannica Encyclopedia of World Religions, Chicago: Encyclopedia Britannica. 2006 (5) 1ሃይማኖተ አበው ዘአትናቴዎስ ገፅ-55 (6) ሃይማኖተ አበው ዘአትናቴዎስ ገፅ-81
@Natiye23
2 ай бұрын
በነካው እጅ ኦሪት/ ዘፍጥረት ምዕ1/26
@The-lj7yh
2 ай бұрын
ማሻአሏህ ተነግረውም አይገባቸው
ወገን እርግጠኛ ነኝ መልስ ነው ብለክ ባቀረብከው አፍረክ መሆን አለበት መልስ፡፡፡መልስ ያልመለስከው አሁንም ተማሩ ለአንድ ሰው ያለውን ጥንካሬ መግለፅ ከስላሴ ጋር ምን ያገናኘዋል?? ለአን አካል 1000 ስም ይኑረው ከስላሴ ጋር ምን ያገናኘዋል???ም/ቱም ስላሴ እኮ 3 የተለያዩ አካላቶች ናቸው፡፡ ሌላው ቁርአን ውስጥ ያሉት ምዕራፎች ከስላሴ ጋር ምን ያገናኘዋል??ም/ቱም ቁርአን ውስጥ ያሉ ምዕራፎችና አንቀፆች በባይብል ውስጥ ካሉ ምዕራፎችና አንቀፆች ጋር ነው ማውራት ያለብክ፡፡፡ እንደውም አንድ ሙስሊም ክርስትና ልቀበል ቢል የትኛውን ባይብል ነው መቀበል ያለበት???ም/ቱም ባይብል ከአንድ በላይ ነዋ 66 የፕሮቴስታንት 73 የካቶሊክ እና 81 የኦርቶዶክስ ከነዚ የቱን ይቀበል??? የሰዎች እድሜ ከስላሴ ጋር ምን ያገናኘዋል?? ነው ስላሴን በዕድሜ መለካት ተጀምሮዋል??? ለማንኛውም ከራሳቹ ሁኑ ዝም ብላቹ ከመለጠፋቹ በፊት፡፡ ይህ መልስ ነው ብላቹ ካመናቹ ፍርድ ለህሊናቹ፡፡ መልስ እንደሌለው ስታውቁ የቆጡን የባጡን ትቀባጥራላቹ፡፡፡ አሁንም የባይብል እውቀት ካላቹ ለውይይት ዝግጁ ነኝ፡፡፡፡፡፡
Addition be Trinity ayseram multiplication enji 1*1*1=1 be sost akalat yemigelex and Amlak
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
ጨርሰህ ስማ።
ሰውየው ለመረጃ ሳይሆን ፍሎ ለመሰብሰብ ነዉ ያቀረብከው
Silezi 3 negeroch maletim Abat +Lij+menfes kidus Egziabher nw?🙂 Sihtet nw.David tesasitual.
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
እስኪ በእውነት በል? ለካ ተሳስቷል? ወይ ጉ...ድ¡¡¡
@eliashabtamu678
2 ай бұрын
Tsehay ....tikur chikawst tigebalech yale neby ....yzeh amineh ...tekebileh endaleh gin tawkaleh ...????
ለራሳችሁ በደንብ ያልገባችሁ በኮንፈራንስ የታወጀን ጉዳይ ለሙስሊም ለማስረዳት መሞከር ትርፉ ራስን መሸንገል አይሆንም? ሁሉም ባይሆንም ሙስሊሙ ከእናንተ በተሻለ ስለክሪስትናም የራሱንም እመነት አብጠርጥሮያውቃል። እግዚያቤር ቃል ነበር ቃልም እግዚያብሔር ዘንድ ነበር የምለው ላይ የሚነሳውን ጥያቄ አንዳችሁም መመለስ አልቻላችሁም። እስቲ መልሳችሁ መላልሳችሁ በሉትና ፍቱት። የመጀመሪያው ከቃል ውጭ ምንም አልነበረም ነው ያላችሁት። ፈጣሪ ከቃል በላይ ነው። ከዚያ ቃልም ቃል ዘንድ ነበር ያው ያላችሁት which doese not make sense
@hanajusus9060
26 күн бұрын
Am sorry yeraskn mejemrya qbterterk betake melkam nw
አብ+ወልድ+መንፍስ ቅዱስ=?
ምን ዓይነት የሞኝ ትንታነ ነው? በነገራችን ላይ ክርስቲያን የክርስቶስ ተከታዮች ወይም አምሳዮች ማለት እንጅ ሦስት የሆነ አንድ አምላክ ማለት አይደለም። ይህ ሰይጣን አለምን ለማጥፋት የፈበረከው እጅግ ግልጽ የሆነ ቅጥፈት ነው።
@Uvbnn
2 ай бұрын
ሁለቱም የደከሙ ናቸው
ምንድን ነው ምትቀባጥረው እረ ተው ስታሳዝን
@Uvbnn
2 ай бұрын
ይሄን ሰውዬ አታምጣብን አልኩት ግን አይሰማኝም የወረደ ሰው ነው David Woood
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
ቁርአን ላይ ወረደበት አይደል?😁 አየሰዞህ አንድ ቀን ደሞ አንተ ትወርድበታለህ።🥰
አህሏ አንድ ነዉ።ሶስት አምላክ የለም ።ቁርአን 114 ምእራፎች የሉት ክታብ ወይም መፅሐፍ ነው።ለስላሴ ምሰሌ ልተረገው አይመችም ።ከበደ+ሰለሞን+ሰሙኤል=ከበደ ልሆን ይችላል ወይ?መልሱ አይሆንም ምክንያት ከበደ ኢድሜው 35 ራጅም ቀይ ሰለሞን ኢድሜዉ 50 ወፍራም እና ሰሙኤል ደግሞ አጭር ፉንጋ ...ወዘተ በእናንተ አባበል እነኚህ ሶስት ሰዎች የተለያየ ማንነት የተለያየ መልክ ፣ቁመና የለቸዉን ሰዎች አንድ ናቸዉ እንዳ ማለት ነዉ። አሏህ ደግሞ ብጤ፣አምሳያ የለኝም ብለዋል።የማንንም ድጋፍ ፣እርዳተ የመይሻ አምላክ ነዉ። ኣይ አለዉ ብለክ ሞቼ እገኛለሁ ከልክ መብትክ ነዉ።ዉጤቱን የፍርዱ ቀን።ቁርአን ኢንዲህ ይላል በአይማኖትም ላይ መስገዳድ የለም የምሬት መንገድ ከጥመት መንገድ ለተገለጠለት ሰው ምእፍ 2:256
Logic እና ክርስትና አብሮ የማይሄዱ ነገሮች ናቸው 😁😁
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
እያየንኮ ነው።
@Uvbnn
2 ай бұрын
@@ewnetyasarfal መፃፍ ቅዱስህ logic ተጠቀሙ ተብላችሁ የተነግራችሁ መሰልኝ
😂😂1 ሲደማር 1ሲደማር 1 ሲደማር 3 አላቃ
This is devid who is defeated by the legend sheikh utsman and brother muhammed hijab many many times 😂😂😂😂
Ende Muhammed yale mirt durye tayito ayitawekim, aye ye ayesha bal....
@bilchasurur857
2 ай бұрын
ስዳደግ ስለእርሳቸው ትንሽ እንካ ግንዛቤ የለክም። ስለእርሳቸው ማወቅ ከፈለክ ጎግል ግባና who is prophet mohammed በልና ሰርች አርግ ። ውዱን ነቢይ ለሰደበ አሏህ ከበድ ቅጣት እንደ ምቀጣው ላሰውቅክ እወደለሁ።
ኧረ ንቁ ብቻውን የሚጮህ ሰው አትስሙ እስኪ ከነ ዶክተር ሸቢር አሊ ጋ ያደረገውን ዲቤት እዩት እውነትን ፈልጉ!!!!
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
አይተነዋል። ጥሩ ውይይት ነው። አንተ ግን በደንብ የሰማከው አይመስለኝም፣ ደግመህ ስማው።
ጅላጅል ሁላ ዝምብላቹ ተጃጃሉ 3ቱም አንድ ነው 😂😂😂
@ewnetyasarfal
2 ай бұрын
የመስማት አቅማችሁ ደካማ መሆኑ ግን ይገርመኛል።
@user-fj5ep9oo2p
2 ай бұрын
አንተም ብሎ አዋቂ...ከንቱወች ሁላ
አየ እስልምና እባካችሁ ወደ ብርሃን ኑ ሙሃመድ በሚባል ቂጡን የጣለ ዱርየ የሱ ሳይበቃ ደግሞ ምድራዊ ፍላጎቱን በ አላህ እያሳበበ ሀጥያትን ዝሙትን ያስፍፍ ዱርየ እባካችሁ ሃይማኖት በቤተሰብ ይሉኝታ አትከተሉ ይሄን ሚዲያ ተከታትሎ አሁንም ሙስሊም መሆን ያማረዉ ሰዉ ሃጥያት ወይም ስጋዊ ፍላጎቱን ለማሟላት ቀላሉን መንገድ እየመረጠ መሆን አለበት እባካችሁ ንቁ ከወሲብ አምላክ ዉጡ
@bilchasurur857
2 ай бұрын
አንተ ነህ ትክክልኛ ሃይማኖት ያየዝከው የፈጠረክ ፈጣሪ ማን እንደሆ የጠፈብክ ። ለማነው ምትሰግደው ? ማነዉ ፅድቅክን ምቀበልክ? ወይ ልፋታችሁ
@YohanesdesyeSisay
2 ай бұрын
አላህ ሁለት ቀኝ እጆች ያለዉ ጣወት እደሆነ ታቃለህ ግን ታመልከዋልህ እዴት ላስረዳክ እችላለሁ
1*1*1=1