Gospel of Grace Channel-2

Gospel of Grace Channel-2

በዚህ ቻናል #አራቱ_ወንጌላት (የማቴዎስ፣ የማርቆስ፣ የሉቃስ እና የዮሐንስ ወንጌል ተከታታይ የቪዲዮ ትምህርት ሙሉ ምዕራፎችን በተብራራ መልኩ የሚቀርብበት ሲሆን ከብሉይና ከሐዲስ ኪዳን መጻህፍት በማጣቀስ ቀርቧል። ስለዚህ በቅደም ተከተል ወይም የሚፈልጉትን ምእራፍ እንንዲያጠኑ ላቸውን #በጌታ #ፍቅር እንጋብዝዎታለን፡፡
ማንኛም #ጥያቄ ወይም #አስተያየት ካለዎት Comment ላይ ይፃፉልን!!
#Like, #Share በማድረግ #ለሌሎች #ወገኖች #እንዲዳረስ #የበኩልዎን #ይወጡ!!
በተጨማሪም በሚከተሉት ሊንኮች በመጠቀም ለንባብ እና ተለያዩ አገልግሎቶች ይጠቀሙባቸው፡፡
Facebook:- facebook.com/groups/1955471598090940/
Website :- www.ewnetone.com/BTM_PAGES/Doctrine0.php
You Tube Pages
Gospel of Grace Channel 1:- kzread.info/dron/6ZObGNbcGm91Xeql_kgEqQ.html?view_as= #የማቴዎስ_ወንጌል #gospel_of_mathew

👉 የማቴዎስ ወንጌልን በቴሌግራም ቻናል መከታተል ከፈለጉ እነሆ:
t.me/Gospel_of_Grace_Matthew

Пікірлер

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo34088 сағат бұрын

    ወንድሙ በሕይወት እያሌ ነዉ ወይስ መቶ ነዉ ሄሮድስ የወንድሙን ምስት ያገበት?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo34089 күн бұрын

    አሜን አሜን በከበረ ዋጋ ተገኝተን በተዎረደ ስፍረ እንደንገኝ እግዚአብሔር ይጠቢቀን ተበረኩ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo34089 күн бұрын

    በዉስጦት ለይ ስለሌዉ ፀጋ ጌታ ይበረክ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo34089 күн бұрын

    እንቁ ግን ምንድነዉ? መለቴ ልዩ ትርጉም አሌዉ?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340810 күн бұрын

    ግን ጌታችን ኢየሱስ ያንን ምሰሌ ለምንድነዉ የታጠቀመዉ?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340810 күн бұрын

    ስለ እርሾ ያቢረሩልን መቢረሬያ በጠም ግልፅ ነዉ ተበረኩ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340810 күн бұрын

    ጌታ ፀጋን በሙለት ይጨምርሎት ገሼ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340810 күн бұрын

    የሰነፍንጪ ቅንጠት ግን ምንድነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels5 күн бұрын

    ሰናፍጭ (ሙስታርድ) በብዛት እንደ ቅመም የምንጠቀመው ሲሆን መጠኗ ትንሽ የሆነች ልክ እንደ ጎመን ዘር ፍሬዋ ትነሽ የሆነች ማለት ነው።

  • @YomifGemechu-v9i
    @YomifGemechu-v9i22 күн бұрын

    my Jesus

  • @YomifGemechu-v9i
    @YomifGemechu-v9i22 күн бұрын

    tebarek wendimachin iyandandun kifil iyetebareknibet new

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340827 күн бұрын

    ቢቻ እግዚአብሔር ይበርኮት የስልክ ቁጡሮትን ፈልጌ ነበረ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels24 күн бұрын

    +251 911772186 ወንድም ግርማ በቀለ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340827 күн бұрын

    ሸክሜ ልዝቢ ስል ቀለል ነዉ መለቱ ነዉ ወይስ ሌለ ፍች አሌበት ?? ሌለ ደሞ ቀንበሬም ቀልል ነዉ ስል ቀለል ነዉ አይከቢድም እያሌ ነዉ???

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels22 күн бұрын

    ማቴዎስ 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁹ ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ³⁰ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና። ልክ ነሽ። ቀላል መሆኑ ከምን አንጻር ነወ? የሚለውን ስናይ ሰዎች በራሳቸው ስራና ጥረት ድካም የእግዚአብሔርን መንግስት መግባት አልቻሉም። ስለዚህ ጌታ በጸጋ የምንድንበትን አዲስ ኪዳን ሰጠን ይህ ነው ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜ ቀላል ያረገልን ከጌታ እንጂ ከእኛ ከይደለም። ስለዚህ መጽሐፍ እንዲህ አለ 👉 ሮሜ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁰ ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና። ²¹ አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ ²² እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ ²³ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ 👉 ²⁴ በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉና፤

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340827 күн бұрын

    እግዚአብሔር ዘመኖትን ጨርሶ ይበርክ የእዉነት በጠም እግዚአብሔር እያስተመረኝ ነዉ እርሶን በመጠቀም

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340827 күн бұрын

    አንበጠ ግን በዝ በኛ ዘመንም ይበለል ወይስ መጥመቁ ዮሐንስ ቢቻ ነዉ የበለዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels24 күн бұрын

    እንደየ አከባቢው ቢለያይም አንበጣን የሚመገቡ ሰዎች አሁንም አሉ።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340824 күн бұрын

    @@GospelofGrace4gospels አንበጠ ግን ምን ነበረ?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340824 күн бұрын

    @@GospelofGrace4gospels ሌለኛዉ ዎሰኝ ጥያቄ ፈርሰዉያን ቢዙም ግዜ ከኢየሱስ ገረ የመይስመሙት ከመጀመሬያዉም ክፉኦች ነቻዉ ወይስ ኢየሱስ ከመጠ ቧሀለ ነዉ ክፉኦች የሆኑት?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels24 күн бұрын

    @@mihretmamo3408 አንበጠ ማለት (locust) በኛ ከፌንጣ ጋር የሚመሳሰል ቅጠሎችን የሚመገብ ነፍሳት ነው።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340824 күн бұрын

    @@GospelofGrace4gospels አመሰግናለሁ እሺ ስለ ፈርሰዉያን ጥያቄ ጠይቄ ነበረ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340828 күн бұрын

    ኢየሱስ ለምንድነዉ ዮሐንስን ከዘች ከሌበት መከረ ደርሶ ያለዎጠዉ እና እስክሞት ድረስም ዝም ያሌዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels5 күн бұрын

    የዮሐንስ አገልግሎት ለጌታ መንገደ ማስተካከል ከጌታ አገልግሎተ በፊት ሰዎችን ወደንስሐ መመለስ እና ለንጉሡ (ለኢየሱስ) የሰዎችን ልብ መመለስ ነው። “የአዋጅ ነጋሪ ቃል፦ የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ፥ ለአምላካችንም ጐዳና በበረሀ አስተካከሉ።” - ኢሳይያስ 40፥3 ነገር ግን በእስራኤል ያንያህል ተቀባይነት ሳያገኝ መንገዱን የሚያስተካክልለት መሲህ (ኢየሱስ) አገልግሎቱን ጀመረ። ዮሐንስ በሄሮድስ እጅ ተይዞ ሳለ ወደጌታ መልእክተኛ ልኮ ነበር። የተሰጠው መልስ ኢየሱስ እያደረጋቸው የነበሩትን ድንቆችን እንዲነግሩት ነው ጌታ መልስ የሰጠው። የዮሐንስ አገልግሎት ተጠናቋል። ሥራው በኢየሱስ ተተክቷል። ይሁን እንጂ እስራኤል በሙላት አልተቀበለችም። ከሶስት አመት አገልግሎት በኋላ ደግሞ ኢየሱስ ያለምንም ጥፋት በመስቀል ላይ በመከራ እንዲሞት ሆነ። ለኛ መዳን ቢሆንልንም ዮሐንስን የገደሉት ኢየሱስንም ገለውታል። የዮሐንስ የተላከበትን ሥራ ሲጨርስ ሞተ። ኢየሱስም የተላከበትን ሥራ ሲጨርስ ሞቷል። ዋናው ምክንያት እሰስራኤል አልተቀበለችም አላመነችም። መድሐኒቷን አዳኟን ገፋች። ከዛም ሐዋርያትንም ገደሉ እስካሁን ድረስ ሰዎች ስለኢየሱስ ይሰደዳሉ። ይገደላሉ። ጌታ እስኪመጣ ድረስ ይቀጥላል። ነገርግን በአንድ ቃል እንጽናናለን። “ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።” - ማቴዎስ 10፥28

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340828 күн бұрын

    በወንጌለት ለይ ቀድሞ የተፀፈዉ የመነዉ?? በሁሌተኛ የተፀፈዉ የመነዉ? በሶስታኛ የተፀፈዉ የመነዉ? በአረተኛስ የተፀፈ የትኛዉ ነዉ መለቴ ወንጌለት??

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels19 күн бұрын

    በመጻህፍቱ የአጻጻፍ ቅደም ተከተል በመጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ የተጻፈ ባይኖርም ከመጽሐፎቹ ይዘት አኳያ አሁን ያለው የአራቱ ወንጌላት አቀማመጥ (ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ እና ዮሐንስ) ወንጌል ብዙ የጥንት አባቶች ይስማማሉ። ዋናው ስለወንጌል መጽሐፍት ማወቅ ያለብን ነገር የመጽሐፎቹ ጸሐፊዎች እና የመጽሐፉ ይዘት ነው። 👉የማቴዎስ ወንጌል የኢየሱስ ክርስቶስን ለእስራኤል የሚመጣው ንጉሥ አድርጎ የትውልድ ሐረጉን ከንጉሥ ዳዊት በመጀመር በነቢያት የተነገረውን የአይሁድ ንጉሥን በማስተዋወቅ ከአይሁድ ለሆኑት በሐዋርያው ማቴዎስ የተጻፈ ነው። 👉 “ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል፦ የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።” - ማቴዎስ 2፥1-2 “ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።” - ማቴዎስ 27፥37 👉 የማርቆስ ወንጌል የጌታ ኢየሱስን አገልጋይነት እንደ ባሪያ አጉልቶ የሚያቀርብ ሲሆን ጸሐፊው ማርቆስ የተባለ ከሐዋርያት ጴጥሮስ እና ጳውሎስ እግር ስር ያደገ ሰው ነው። 👉 የሉቃስ ወንጌል ደግሞ ኢየሱስን የሰው ልጅ ወይም ሥጋ የለበሰ አምላክ አድርጎ የሚያቀርብ ሲሆነ የኢየሱስን ልደት እና የትውልድ ሐረግ በእናቱ በኩል እስከ አዳም በመቁጠር የሚጀምርና የአየሱስን የሰው ልጅ አድርጎ በማጉላት ሉቃስ በተባለ ከአህዛብ ወገን በሆነ የተማረ እና ባለመድኃኒቱ ሉቃስ ሲሆን ከጳውሎስ ጋር ብዙ የሰራ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍንም የጻፈ ነው። 👉 የዮሐንስ ወንጌል በሐዋርያው ዮሐንስ የተጻፈ ሲሆን ከሶስቱ ወንጌላት ለየት ባለ መልኩ የኢየሱስን መለኮታዊ ማንነቱን አጉልቶ የሚያሳይ ሲሆን ሶስት መልእክታት እና የራእይ መጽሐፍን ጽፏል። በተጨማሪ የአዲስ ኪዳን መጻህፍትን በተመለከተ የዚህ ተከታታይ ትምህርት ሲጀመር የተሰጡ 6 ተከታታይ ትምህርቶችን ብታይው በጣም ይጠቅምሻል። በተረፈ በርቺ በዋትስአፕ የተሻለ መጻጻፍ እንችላለን። ጸጋ ይብዛልሽ። kzread.info/head/PLKCdy0KEwU7BblINMMQcO6DSHlphTe6fQ&si=KSM9e0wVStaCX-uL

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340828 күн бұрын

    መጥመቁ ዮሐንስ ወዴ ኢየሱስ የለከቻዉ ሁሌቱ ደቀ መዘሙርት የረሱ ደቀ መዘሙርት ነቻዉ ወይስ የኢየሱስ ደቀ መዘሙርት ነቻዉ???

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels24 күн бұрын

    “ኢየሱስም አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርቱን ማዘዝ በፈጸመ ጊዜ በከተሞቻቸው ሊያስተምርና ሊሰብክ ከዚያ አለፈ።” - ማቴዎስ 11፥1 ጌታ የራሱን ደቀመዛሙርት ለወንጌል አገልግሎት ካዘዛቸው በኋላ የዮሐንስ ሁለቱን ላከ። እነዚህ ሁለት ደቀመዛሙርት የዮሐንስ የራሱ ናቸው።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340828 күн бұрын

    ምህረፍ አስር ለይ አንድ ያልገበኝ ቦታ አሌ ጠሼ ማቴዎስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁴ በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ³⁵ ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ³⁶ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። ምን መለት ነዉ?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo340824 күн бұрын

    ጥያቄ ይመለስልኝ

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels24 күн бұрын

    ማቴዎስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³⁷ ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ³⁸ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ³⁹ ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። 👉ሉቃስ 21 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁶ ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤ ¹⁷ በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ። ¹⁸ ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤ 👉👉 በትምህርቱ እንደተገለጠው በዚህ ክፍል ጌታ ሰለ ሰላም የተናገረው እኛ ጌታን ስንቀበል እና የእሱን መንገድ ስንጀምር ከቅርብ ወዳጆች ከቤተሰብም እናት አባት ወንድም እህት እኛን ለሚያሳድዱን አሳልፈው እንደሚሰጡን በወንጌል በማመናችን በዚህች አለም ብዙ ጠላት እንደሚበዛብን እና በመከራውም ጌታን አክብረን እንድንኖር እንጂ ፈርተን ወደኋላ እንዳንመለስ ከነዚህ ጌታን ከማይቀበሉ ጋር ህብረት ሊኖረን እንደማይገባን፤ ለዘመድ ወዳጅ ብለን ጌታን መተው እንደሌለብን፤ ለማስረዳት ጌታ የተጠቀመበት ትምህርት ነው። ከማያምኑ ጋር ግልጽ ልዩነት መኖሩን እንረዳለን። 👉“ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?” - 2ኛ ቆሮ 6፥14 ጌታ እዚህ ላይ ያነሳው ሐሳብ በአማኝ ላይ ከሚነሳው ተቃውሞ አንጻር ሲሆን 👉ጌታ የሰላም አምላክ፣ ንጉሥ፣ አለቃ ነው እኛም ምንም እንኳ ብንገፋም ቢጠሉንም የሰላም ሰባኪዎች ሆነን መገለጥ ይኖርብናል። ጌታ ሰላማችን ነው። “እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥” - ኤፌሶን 2፥14-15 እህቴ ግልጽ ካልሆነ እንደገና እናየዋለን። ስለዘገየሁ ይቅርታ። በርቺ!

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ድንቢጦች የምለዉ ምንድነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ድንቢጥ በጣም ትንሿ ወፍ ስትሆን ብዙ ጊዜ በግቢ ውስጥ ትገኛለች።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels እሺ እንዴዘ ያሌዉ እና በሱ የመሰለዉ ምን ለመለት ነዉ

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels27 күн бұрын

    በወቅቱ የድንቢጦች እንኳ ዋጋ አላቸው እናንተ ግን ከድንቢጥ ትበልጣላችሁ ለማለት ያቀረበው ምሳሌ ሲሆን ጌታ ሲያስተምር ምሣሌዎች የሚጠቀምበት ሁኔታ የሰሚዎቹን የመረዳት አቅም በመረዳት ነው። ጌታ እናንተ ከድንቢጦች ትበልጣላችሁ በማለት ያጽናናበት ምሣሌ ነዉ። 👉 ማቴዎስ 10 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁹ ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ከእነርሱም አንዲቱ ያለ አባታችሁ ፈቃድ በምድር ላይ አትወድቅም። ³⁰ የእናንተስ የራሳችሁ ጠጉር ሁሉ እንኳ ተቈጥሮአል። 👉 ³¹ እንግዲህ አትፍሩ ከብዙ ድንቢጦች እናንተ ትበልጣላችሁ።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ሰመዕተት መለት ምን መለት ነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ሰማዕት ማለት በወንጌል ምክንያት መገደል ማለት ነው ዋናው ሐሳብ። (“የዮሐንስንም ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው።”) - ሐዋርያት 12፥2

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels ok መገደል የመለት ሌለ ትርጉሙ ነዉ ስማዕት መለት።?

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ok ያ ለደቀ መዘሙርቶቹ የተነገረቻዉ ነገሮች ሁሉ ያ መከረ ሁሉ በነርሱ ዘመን መለቴ ያኔ በነበሩት ደቀ መዘሙርት ግዜ ያልተፈፀመ ለወዴፍት የምፈፀም መከረ ነዉ መለት ነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ልክ ነሽ ያው የወንጌል አገልግሎት ሁሌም መከራ ይበዛዋል። 👉“በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።” - ዮሐንስ 16፥33 የክርስቲያኖች ኑሮ በብዙ መከራ የታጀበ ነገርግን በጌታ አሸናፊዎች ነን። በዚያን ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ የተናገረው ዛሬም በእኛ ድረስ አለ። ❤የጌታ ጸጋ እና ሰላም ይብዛልሽ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels አሜን አሜን አሜን ተበረኩልኝ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    እሺ አበት እግዚአብሔር ይበርኮት እና ጌታችን የቅሰርን ለቅሰር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ ስል ለእግዚአብሔር የምሰጠዉ የምን ምስል ያሌበት ነዉ?? መለቴ የቅሰር ምስል ያሌዉን ለቅሰር ስለሌ ነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    የሄ አገላለጽ ከጠያቂዎቹ ፍላጎት አንጻር ስናየው ወቅቱ እስራኤል በሮም መንግስት አስተዳደር ስለነበረች አይሁዶች ተገደው ይተዳደሩ ነበር። ስለዚህ ለሮም መንግስት ግብር መክፈል ወይም መተባበርን እንደ ነውር ስለሚቆጠር በጌታ ላይ የመክሰሻ ምክንያት ለቄሳር ግብር መክፈል ይቻላል ወይስ አይቻልም? ይህም ለቄሳር ይከፈል ቢል በአይሁድ ሊከሱት፤ አይከፈልም ቢል በመንግስት (ቄሳር) ሊከሱት ፈልገው ነበር። ጌታ ልባቸውን ስለሚያውቅ በዚህ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ አለ። በሣንቲሙ ላይ ያለውን መልክ እንደምሳሌ ተጠቀመው እንጂ ለቄሳር ም የሚሰጠው በወቅቱ የገንዘብ ነው ያው ሀእግዚአብሔርም የሚሰጠው የዚያው ጊዜ የሚገበያዪበትን ሣንቲም ነው የሚሰጠው እንጂ የተለየ ሣንቲም አይደለም። አባባሉ ለቄሳርም ግብር ክፈሉ የጌታንም መባ ወይም በዚያ ዘመን አሥራት ስጡ ለማለት ነው።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    እግዚአብሔር ዘመኖትን ጨርሶ ይበርክ ሌለ ግልጠትን ይጨምርሎት አበቴ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    እግዚአብሔር ይበርኮት አበቴ ታበረኩ እና ቦአርኔጌር የምለዉ የነጓድጓድ ልጆች ያሌዉ ኢየሱስ ከመከከለቻዉ የተዎሰኑ ሰዎችን ነዉ ወይስ 12ቱንም ነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    የነጎድጓድ ልጆች የሚባሉት ሁለቱ ዮሐንስና ያዕቆብ ብቻ ናቸው።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels ልዩ ስም የተሰጠለቻዉ ለምንድነዉ? መለቴ ለያት የምአደርገቻዉ ነገር አሌ

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels የነጓድጓድ ልጆችስ ለምለዉ ቀል ሌለ ፍች አሌ መለቴ ለመለት የፈለገዉ ምንድነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ይህ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው በዚህ ቦታ ብቻ ስለሆነ ሰፋ ያለ ፍቺ ማግኘት አይቻልም። ነገር ግን በዚህ ቦታ በተገለጸበት ሁኔታ የሁለቱ ወንድማማቾች የአገልግሎት ጠባይ የሚያሳይ ነው። ለምሣሌ ከ12ቱ ሐዋርያት ያዕቆብ የመጀመሪያው ሰማዕት ሲሆን (“የዮሐንስንም ወንድም ያዕቆብን በሰይፍ ገደለው።” ሐዋርያት 12፥2) ዮሐንስ ደግሞ አስከ ራዕይ መጽሐፍ ፍጻሜ ድረስ የቆየ ምናልባትም በህይወት የቆየው የመጨረሻው ሐዋርያ ነው። በዚህ ምዕራፍ ሐዋርያትን ሁለት ሁለት አድርጎ ወንጌል እንዲሰብኩ ሲልካቸው "የነጎድጓድ ልጆች" ብሎ መሰየሙ፤ ለወንጌል ስራ ያላቸውን ከፍተኛ ተነሳሽነት አውቆ እንደሆነ "ቦአኔርጌስ" ከሚለው የቃሉ ፍቺ መረዳት ይቻላል። ሀይለኛ እና ተጽእንኖ ፈጣሪ የሆነ ስብከታቸው ሊሆን እንደሚችል ይታመናል። (zealous and vigorous nature of James And John ) የነጎድጓድ ልጆች ሲል 👉ነጎድጓድ የሚለው ስም የወላጅ አባታቸው ተለዋጭ ስም ሳይሆን ጌታ ራሱ የሰየመው ስም መሆኑ ከላይ የገለጽኩልሽን ትርጉም የበለጠ ይገልጸዋል።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels ወዉ በጠም ደስ በምል አገለለፅ ነዉ የገለፁልኝ ከልቤ አመሰግናለሁ ዘመኖት ይለመልም ተበረኩ ግን ለበለጠዉዉ መረደት የዋትሰፒ ቁጥር ቢኖርና ቢሰጡኝ ደስ ይለኝ ነበረ ምክንያቱም ለ12 ሰዎች ሆነን ማቴዎስን እያጠነን ነበረ ቢዙ ያልገቡልን አሰቦች ስለሉ ልንጠይቆት እንፈልገሌን

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ንደድ ግን ምን ነበረ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    በቅድሚያ እንኳን ደህና መጣሽልን❤ ንዳድ ማለት የወባ የሚመስል በጣም የሚያተኩስ ህመም ነመ፡

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    “በእግራቸው እንዳይረግጡት ተመልሰውም እንዳይነክሱአችሁ፥ የተቀደሰውን ለውሾች አትስጡ፥ ዕንቁዎቻችሁንም በእሪያዎች ፊት አትጣሉ።” - ማቴዎስ 7፥6 እሄ ቦታ ምን ለመለት ነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ይህ አይነት አገላለጽ ፈጽሞ ለወንጌል የማይታዘዙ ሰዎች የምንነግራቸውን ቃል ከማመን ይልቅ ለሰድብና ሌሎችም እንዳይሰሙ ስለሚያደርጉ ስለማይጠቅማቸው የተወሰነ ምስክርነት ከሰጠናቸው በኋላ ብዙ ክርክር አለማድረግ የሚሰሙትን ቃል ሁሉ ለክፋት ስለሚያውሉት ከእንደዚህ አይነት ሰዎች እንራቅ ምንም ጥሩ ነገር ብናቀርብላቸው ተመልሰው ከፌዝና ስድብ አይወጡም። ማቴዎስ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵⁶ እኅቶቹስ ሁሉ በእኛ ዘንድ ያሉ አይደሉምን? እንኪያስ ይህን ሁሉ ከወዴት አገኘው? ተሰናከሉበትም። ⁵⁷ ኢየሱስ ግን፦ ነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ቤቱ በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው። ⁵⁸ በአለማመናቸውም ምክንያት በዚያ ብዙ ተአምራት አላደረገም።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ግን ኢየሱስ በተለያዩ ቦተኦች ስፈዉሰቻዉ ለመንም አተሰይ ተጠንቀቅ ቢሎ ስነገርም የተፈዎሱት የደኑት ግን ዎጥቶ ስነገሩና ስመሰክሩ እነያሌን??

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    እነዚህ በስጋቸው ያለ በሽታ የተፈወሰላቸው ሁሉ እውነተኛ አማኞች አይደሉም። ኢየሱስ ለማንም አታሳዩ የሚልበት ምክንያት ነገሮችን በራሱ ጊዜ መግለጥ ስለሚፈልግ እና ለማይገባቸው የጊዜው ሰዎች ውስጣቸውን ስለሚያውቅ እንዲየውም ፈውሱን ሊከሱበት እንደመረጃ ለሚሠበስቡ የጊዜው የሀይማኖት መሪዎች ፍርድ ሲሆን እነሱን ራሳቸውንም የሚፈትንበት መንገድ ነው።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ቢዙ ጥያቄኦች አሉኝ እና ዋትሰፒ ቁጡር ከአሌ ቢትልኩልኝ በጠም አርፍ ነዉ

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ተባረኪ እህቴ እንልክልሻለን።

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    በመቀጠል በማቴዎስ በምህረፍ 6፥3/4 ለይ ለምፀሙን ፈዉሶ ቧሀለ ለመንም እንደትነገር ቢሎ ያስጠነቀቀ ለምንድነዉ?

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospelsАй бұрын

    ጌታ የሁሉን ልባቸውን ስለሚያውቅ በምልክቶች ብቻ የሚየመደንቁ እንጂ በምልክቶቹ የማያምኑ ስለሆነ ለሚመለከታቸው ካህናት ብቻ አሣይ አለው። የዚህ አይነት ሐሳቦች በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ቦተዎች ላይ አለ። እያዩ ለማያምኑት ፍርድ ነው። የልባቸውን የሚያውቅ ጌታ ለማይገባቸው ሰዎች አትንገር አለው፥ ቢነግራቸውም አይጠቅማቸውምና ነው። ዋናው ሐሳብ ፍርድን ያመለክታል

  • @mihretmamo3408
    @mihretmamo3408Ай бұрын

    ሰለምና ፀጋ በእጥፍ ይቢዘሎት የተከበሩ የእግዚአብሔር አገልገይ ስለ ሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይበርኮት

  • @GgHh-bt9cs
    @GgHh-bt9cs2 ай бұрын

    ❤🎉www ooww

  • @danieldangiso8642
    @danieldangiso86422 ай бұрын

    Ameen!!

  • @meazakassa9899
    @meazakassa98993 ай бұрын

    31 ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ኃጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል፥ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ አይሰረይለትም። 32 በሰው ልጅ ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለም ቢሆን ወይም በሚመጣው አይሰረይለትም።

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels3 ай бұрын

    @highlite

  • @RealBiblerevelation
    @RealBiblerevelation4 ай бұрын

    ❤#10ቱ_ቆነጃጅቶች_እነማን_ናቸው?❤ ================================= ✍️ብዙ ሰባኪዎች በማቴዎስ 25፡1-13 ያለውን ክፍል በማንሳት እውነተኛ አማኞችን እንደሚመለከት አድርጎ በማስተማር ቅዱሳንን ከየትኞች ናችሁ ከሰነፎች ወይስ ከብልሆች ወዮላችሁ በማለት ክፍሉን ያለቦታው በመጥቀስ ቅዱሳንን ግራ አጋብተዋል። ከዚህም የተነሳ ክፍሉም በአማኞች ውስጥ ግራ መጋባትን የፈጠረ ክፍል ሆኖ ይገኛል። ✍️ጥያቄ በመጠየቅ እንጀምር፦ ----------------------- 📌በማቴዎስ 25 ላይ የተጠቀሱት ቆነጃጅቶች እነማን ናቸው?? 📌እውነት ክፍሉ ቤተክርስቲያንን(አማኞችን) ይመለከታል?? 📖 መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል፦ ======================= ✍️ይህ ክፍል ሐዋርያቶች በጠየቁት ጥያቄ መሠረት ጌታ ኢየሱስ በምሳሌ ከመለሳቸው መልሶች አንዱ ነው። 📌ማቴዎስ 24 (Matthew) 3፤ እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው፡- ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት። ✍️መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንን(ቅዱሳንን ሁሉ) ይዞ ሲሄድ የቤተክርስቲያን መነጠቅ ይሆናል። ከዛም በኃላ በምድር የ7 ዓመት የመከራ ዘመን ይሆናል። የመጀመሪያው ሶስት አመት ተኩል በማቴዎስ 24 መሠረት የምጥ ጣር መጀመሪያ ይባላል። በሁለተኛው ሶስት አመት ተኩል በማቴዎስ 25 መሠረት ታላቁ የያዕቆብ (የእስራኤል) መከራ የሚባለው ይሆናል። ✍️ ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ለመንገስ ከመምጣቱ በፊት በ7 ዓመቱ የመከራው ዘመን ስለ መሲሁ የሚመሰክሩ ሁለቱ ወይራዎች የሚባሉ አሉ ራዕ 11:4 ። እነዚህ ሰዎች በሙሴና በኤልያስ መንፈስ የሚያገለግሉ ሲሆኑ የሚሰብኩትም የመንግስት ወንጌል ነው። ይህ የመንግስት ወንጌል ሰዎችን በዋናነትም እስራኤላውያንን ለንጉሱ ለኢየሱስ የሚያዘጋጅ ወንጌል ነው። በእነዚህ ሰዎች ስብከት ወደ 144,000 ሺ የሚሆኑ ወጣቶች ተለውጠው የመንግስት ወንጌልን እስከምድር ዳርቻ ይሰብካሉ ራዕ 7:4 በዛ ሰዓት እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በተመለከተ ለአባቶቻቸው በማለላቸው መሃላ መሰረት ኢየሱስ በዳዊት ዙፋን ላይ በመቀመጥና መናገሻ ከተማውን ኢየሩሳሌም በማድረግ ምድርን ለ1ሺ ዓመት ይገዛል:: (የሺ አመት መንግስት የሚባለው ነው) ✍️ በመከራው ዘመን ይህን የመንግስት ወንጌል ሰምተው የሚያምኑ ሰዎች በማቴዎስ ቋንቋ ብልሆች(በጎች) ሲባሉ የመንግስት ወንጌልን የማያምኑ ሰዎች ደግሞ ሰነፎች(ፍየሎች) ተብለዋል። ✍️በመንግስት ወንጌል ያመኑት ብልሆች(በጎች) ይባላሉ። ኢየሱስ እንዳለው አለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግስት ውረሱ ይላቸዋል ይህም መንግስት የሺህ ዓመት መንግስት የሚባለው ነው። በመንግስት ወንጌል ያላመኑትን ሰነፎች (ፍየሎች) ይላቸዋል። መጨረሻቸው ለሰይጣንና ለአጋንንቶች ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ። ማቴ 25:31-46 ✍️ ልናስተውል የሚገባና እውነት ክርስቲያኖች ከብልሆችም ከሰነፎችም ከበጎችም ከፍየሎችም.... የሉበትም። 📌 ቅዱሳን ልብ ሊሉት የሚገባ ነገር ============================== 1) ይህ የሚፈጸመው የቤተክርስቲያን መነጠቅ ከሆነ በኃላ መሆኑን ልብ ልንል ይገባል። 2) ቤተክርስቲያን ባሏን በናፍቆት የምትጠብቅ ሙሽሪት እንጂ ዘይት ለመግዛት የምትሮጥ ቆነጃጅት አይደለችም። 3) መጥምቁ ዮሐንስ እንደመሠከረው እኛ ሁላችን ሚዜዎች ነን ሙሽሪት ያለችው እሱ ሙሽራው ነው በማለት ሚዜ መሆናቸውንና ስለ ሙሽሮች ስለ ክርስቶስ እና ስለቤተክርስቲያን መስክሯል። 4) አሁን በዚህ ዘመን የሚሰበከው የጸጋ እና የክብር ወንጌል ሲሆን ቤተክርስቲያን ከተነጠቀች በኃላ ባለው 7 የመከራ ዓመታት የሚሰበከው የመንግስት ወንጌል መሆኑን ልብ ልንል ይገባል። 5) የመንግስት ወንጌል ዋነኛ አላማው እስራኤላውያንን ለንጉሱ ለኢየሱስ ማዘጋጀት ነው ኢየሱስም በያዕቆብ ቤት በዳዊት ዙፋን ላይ ለሺ ዓመት በምድር ላይ ይነግሳልና። 6) ይህ የሺ አመት መንግስት ደግሞ አለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተዘጋጀ መሆኑን ልብ ይበሉ። ለእኛ ለክርስቲያኖች ግን ምድርን ሳይሆን ዘላለማዊ መንግሥቱንና ክብሩን ከሁሉ በላይ ራሱን ነው ያዘጋጀልን። 1ጴጥ 1:3-5 ✍️1 ተሰሎንቄ 5 (1 Thessalonians) 1፤ ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤ 2፤ የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና። 3፤ ሰላምና ደኅንነት ነው #ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት #ይመጣባቸዋል ከቶም #አያመልጡም። 4፤ #እናንተ_ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ #በጨለማ_አይደላችሁም፥ 5፤ ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤ ✍️1 ተሰሎንቄ 5 9፤ እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ። ✍️ 2 ቆሮንቶስ 13፡14 የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።

  • @RealBiblerevelation
    @RealBiblerevelation4 ай бұрын

    ይህ ክፍል ስለ ቤተክርስቲያን ነውን? በእውኑ ቤተክርስቲያን አምስት ወይም አስር ቆነጃጅቶች ናት ?ወይስ አንዲት ሙሽራ ናት ? ደግሞ አምስቱ ዘይት አሊያዙም አምስቱ ይዘው ነበር በለዋል ታዲያ መጀመሪያ ሳይኖራቸው እንዴት ዘይቱ አለቀባቸው ዘይት=መንፈስ ቅዱስ ይሁን እሽ ግን ከየት ነው ዘይቱ ሚገዛው ገዙ ስለሚል። መምህር ፀጋ ይብዛሎት ግን ነገሩ እንደዚህ አይመስለኝም በቀጣይ 10ቱ እነማናቸው ሚሉትን ጽሑፍ እስቲ ያንብቡልኝ ከእርሷ በላውቅም።

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels3 ай бұрын

    ማቴዎስ 25 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ በዚያን ጊዜ መንግሥተ ሰማያት መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ሊቀበሉ የወጡ አሥር ቆነጃጅትን ትመስላለች። ² ከእነርሱም አምስቱ ሰነፎች አምስቱም ልባሞች ነበሩ። ³ ሰነፎቹ መብራታቸውን ይዘው ከእነርሱ ጋር ዘይት አልያዙምና፤ ⁴ ልባሞቹ ግን ከመብራታቸው ጋር በማሰሮአቸው ዘይት ያዙ። ⁵ ሙሽራውም በዘገየ ጊዜ ሁሉ እንቅልፍ እንቅልፍ አላቸውና ተኙ። ⁶ እኩል ሌሊትም ሲሆን፦ እነሆ፥ ሙሽራው ይመጣል፥ ትቀበሉት ዘንድ ውጡ የሚል ውካታ ሆነ። ⁷ በዚያን ጊዜ እነዚያ ቆነጃጅት ሁሉ ተነሡና መብራታቸውን አዘጋጁ። ⁸ ሰነፎቹም ልባሞቹን፦ መብራታችን ሊጠፋብን ነው፤ ከዘይታችሁ ስጡን አሉአቸው። ⁹ ልባሞቹ ግን መልሰው፦ ምናልባት ለእኛና ለእናንተ ባይበቃስ፤ ይልቅስ ወደሚሸጡት ሄዳችሁ ለራሳችሁ ግዙ አሉአቸው። ¹⁰ ሊገዙም በሄዱ ጊዜ ሙሽራው መጣ፥ ተዘጋጅተው የነበሩትም ከእርሱ ጋር ወደ ሰርግ ገቡ፥ ደጁም ተዘጋ። ¹¹ በኋላም ደግሞ የቀሩቱ ቈነጃጅት መጡና፦ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ፥ ክፈትልን አሉ። ¹² እርሱ ግን መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ አላውቃችሁም አለ። ¹³ ቀኒቱንና ሰዓቲቱን አታውቁምና እንግዲህ ንቁ።

  • @Wudeeee
    @Wudeeee4 ай бұрын

    ❤❤❤❤

  • @Eluuser-dx5ui5uk3f
    @Eluuser-dx5ui5uk3f4 ай бұрын

    ameen ✅️

  • @Wudeeee
    @Wudeeee4 ай бұрын

    እንደዝ ያለ እውቀት ያላቸው ሰዎች ግን ለምንድነ የመይታወቁት እግዚአብሔር ይበርኮት

  • @messengerofjesus-sw9yp
    @messengerofjesus-sw9yp5 ай бұрын

    🙏🙏🙏

  • @Abgirm
    @Abgirm6 ай бұрын

    ጸጋ ይብዛልህ። ወንድሜ።

  • @brtukanmatewos5855
    @brtukanmatewos58556 ай бұрын

    ተባረክ 2×) እግዚአብሔር አባት ሙት የነበርነውን ላረከን ሕያዋን በክርስቶስ ወልደህ ሕይወት ሰጥተሀናል አንተ ባለህበት ልንኖር በቅተናል❤📖❤

  • @brtukanmatewos5855
    @brtukanmatewos58557 ай бұрын

    የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ ውድ ወንድሞቼ❤📖❤🙏🙏🙏😍😍😍

  • @brtukanmatewos5855
    @brtukanmatewos58557 ай бұрын

    የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ😍📖❤🙏

  • @melkam9917
    @melkam99178 ай бұрын

    ወንድሜ ወንጌልን ብቻ የምትሰብክ ታማኘ አገልጋይ ንህ፡፡ ብዙ አስተምረህኛል ተባረክ!!

  • @Abgirm
    @Abgirm8 ай бұрын

    🙏🙏🙏

  • @brighttube777
    @brighttube77710 ай бұрын

    ❤❤❤❤

  • @fikru-xe8iv
    @fikru-xe8iv10 ай бұрын

    be blessed FOREVER pls do teachings on TRINITY

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels10 ай бұрын

    Thankyou Brother, you can get on telegram channel ' Gospel of grace media ' or we will post soon in our youtube channel 1 ==> @GospelofGraceChannel1

  • @fikru-xe8iv
    @fikru-xe8iv10 ай бұрын

    @@GospelofGrace4gospels ok tnx God bless you tnx ❤️❤️❤️❤️❤️🙏❤️🙏❤️🙏❤️🙏❤️

  • @fikirtegegne2831
    @fikirtegegne283110 ай бұрын

    ፀጋ ይብዛልክ ❤

  • @fikru-xe8iv
    @fikru-xe8iv10 ай бұрын

    be blessed forever again and again forever ❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️

  • @GospelofGrace4gospels
    @GospelofGrace4gospels10 ай бұрын

    Dear Fikru. I Iost your comment after I share a telegram link Please you can get the TRINITY lessons on telegram channel " Gospel of grace media" or I will post on our First youtube channel soon. " @gospelofgracechannel1 " let me know if you get.