የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች ኒያሜይ የሚገኘውን የኒጀር ጦር ሰፈር ለቀው ወጡ

የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሜይ ከሚገኘው የጦር ሰፈራቸው ሙሉ ለሙሉ ለቀው መውጣታቸውን እና በስተሰሜን ከሚገኘው አጋዴዝ የጦር ሰፈር ደግሞ እስከ መስከረም 5 ድረስ ለቀው እንደሚወጡ፣ ሁለቱም ሀገራት እሁድ እለት አስታውቀዋል።
የኒጀር ወታደራዊ መሪዎች እ.አ.አ በሐምሌ 2023 ባካሄዱት መፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከተቆጣጠሩ በኃላ መጋቢት ወር ላይ ከዋሽንግተን ጋር የነበራቸውን ወታደራዊ ትብብር ስምምነት አቋርጠዋል።
ዩናይትድ ስቴትስ በአጋዴዝ አቅራቢያ የሚገኘውን ዋና የድሮን ሰፈር ጨምሮ፣ በምዕራብ አፍሪካ በሚገኙ በርካታ የሳህል ሀገራት የሚካሄዱ ፀረ-ጂሃዲስት ተልዕኮ አካል የሆኑ ወደ 650 የሚጠጉ ወታደሮች ኒጀር ውስጥ ነበሯት።
ሁለቱ ሀገራት ባወጡት መግለጫ "የኒጀር መከላከያ ሚኒስትር እና የዩናይትድ ስቴትስ መከላከያ ሚኒስትር፣ የአሜሪካ ወታደሮች እና መሳሪያዎቻቸው ከኒያሚ የጦር ሰፈር ሙሉ ለሙሉ ለቀው የመውጣታቸው ሂደት መጠናቀቁን አስታውቀዋል" ብሏል።
የአሜሪካ ወታደሮችን ያሳፈረው የመጨረሻ በረራ እሁድ እለት ከኒያሜይ እንደሚነሳም ተመልክቷል።
- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -
🔷 የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሊንኮችን በመጫን ይከተሉን።
ፌስቡክ - / voaamharic
ኢንስታግራም - / voaamharic
X - / voaamharic
ዌብሳይት - amharic.voanews.com
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ፡- / voaamharic
የስልክ መሥመራችን 202-205-9942 የውስጥ መሥመር 14 ነው።
📜 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።
VOA Amharic reaches our audience on digital, radio, and TV, delivering news and content about Ethiopia, Eritrea, Africa, and the United States. We will also be bringing you Health Shows, Youth Shows, Democracy Field, Women’s Shows, and Sports Shows on different days, stay tuned.

Пікірлер

    Келесі