የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ የሥራ ዘመናቸውን አጠናቅቀው ተሰናበቱ

በኢትዮጵያ የትጥቅ ግጭቶች “ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋና ምክንያት ኾነው ቀጥለዋል” ያለው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በሕይወት የመኖር መብትን አሳሳቢ ማድረጉን፣ ዛሬ ዐርብ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ዶክተር ዳንኤል በቀለ፣ የትጥቅ ግጭቶቹ እያደረሱት ያሉት ዘርፈ ብዙ ሥቃይ “እጅግ እየጨመረ” መኾኑን ገልጸው፣ ብቸኛው መፍትሔ የሰላም ውይይት ነው፤ ብለዋል፡፡
የኮሚሽኑን ሪፖርት ለብዙኀን መገናኛዎች ያቀረቡት ዋና ኮሚሽነሩ ዳንኤል በቀለ፣ የአምስት ዓመታት የሥራ ጊዜያቸውን አጠናቅቀው ተሰናብተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ በዶክተር ዳንኤል በቀለ ዋና ኮሚሽነርነት እየተመራ፣ በዓለም አቀፉ የብሔራዊ ሰብአዊ መብቶች ተቋማት ጥምረት፣ የፓሪስ መርኅዎችን ወይም የተኣማኒነት መለኪያዎችን ለሚያሟሉ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት የሚሰጠውን "A status" ወይም "A ደረጃ" በ2014 ዓ.ም. ታኅሣሥ ወር አግኝቷል።
ዋና ኮሚሽነሩ ዳንኤል በቀለም፣ በቅርቡ የአውሮፓ ኅብረትን የ”ሹማን” ሽልማት፣ እንዲሁም ለሰብአዊ መብቶች መከበር የሕይወት ዘመን አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የሚሰጠውን የጀርመን አፍሪካ ሽልማት ማግኘታቸው ይታወሳል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዐዲስ ዋና ኮሚሽነር እስኪሾም ድረስ፣ በኢሰመኮ መቋቋሚያ ዐዋጅ መሠረት ምክትላቸው ወይዘሮ ራኬብ መሰለ ኃላፊነቱን እንደሚረከቡም ዶክተር ዳንኤል ገልጸዋል፡፡
- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -
🔷 የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሊንኮችን በመጫን ይከተሉን።
ፌስቡክ - / voaamharic
ኢንስታግራም - / voaamharic
X - / voaamharic
ዌብሳይት - amharic.voanews.com
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ፡- / voaamharic
☎️የስልክ መሥመራችን 202-205-9942 የውስጥ መሥመር 14 ነው።
📡 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።
VOA Amharic reaches our audience on digital, radio, and TV, delivering news and content about Ethiopia, Eritrea, Africa, and the United States. We will also be bringing you Health Shows, Youth Shows, Democracy Field, Women’s Shows, and Sports Shows on different days, stay tuned.

Пікірлер: 4

  • @nebiyubirding
    @nebiyubirding4 күн бұрын

    We are doomed!

  • @EthioTourism277
    @EthioTourism2775 күн бұрын

    አሳዛኝ ዜና የዳንኤል በቀለ ከስራ መልቀቅ ለስእራቱ ትልቅ ነጥብ መጣል ይመስለኛል

  • @abbaagoolee4496
    @abbaagoolee44965 күн бұрын

    Daniel Bekele a liyer .. . He is protecting only Amharas . Not Ethiopians .

  • @Yohana02390

    @Yohana02390

    4 күн бұрын

    The suffering of Amhara is untold. Only 5% of the Amhara suffering is disclosed by EHRC. Anyway you'll hear the truth one time.

Келесі