Rasin mawoq | ራስን ማወቅ - በርናባስ ቶማስ

በስመ አብ ወወልድ(ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ) ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
አዳኛችን፣ ንጉሣችን፣ ቤዛችን፣ ታዳጊያችን፣ ዓለታችን፣ መንገዳችን፣ እውነታችን፣ ሕይወታችን፣ ብርሃናችን፣ አስታራቂያችን፣ እረኛችን፣ ሰላማችን፣ ጽድቃችን፣ ቅድስናችን፣ ጌታችን፣ እምነታችን፣ ተስፋችን፣ ደስታችን፣ ዕረፍታችን፣ ንጽሕናችን፣ መሠረታችን፣ ሊቀ ካህናችን፣ መሪያችን፣ ዳኛችን፣ ጻድቅ ፈራጃችን፣ የታረደው የእግዚአብሔር በግ፣ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ፣ የእግዚአብሔር ቃል፣ ሕያው እግዚአብሔር ወልድ፣ አልፋና ዖሜጋ፣ ፊተኛውና ኋለኛው፣ መጀመርያውና መጨረሻው፣ ትንሣኤ፣ ክብራችን፣ ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ፣ በቅርቡ የሚመጣው ቅዱሱ ሙሽራችን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው! አሜን ሃሌ ሉያ!
"ይመጣል። በእርግጥ ይመጣል። አስቀድሞ ግን ምድርን የሚያጠሩ መላእክቶችን ይልካል።
ወቅቱ መንፈስ ቅዱስ ወደ ጸሎት ቤቴ እንድገባና ብቻዬን ዘግቼ እንድጸልይ ትዕዛዝ የሰጠኝ ወቅት ነበር። ገና በንስሐ፣ በኑዛዜና የምልጃ ጸሎቴን ጨርሼ የምስጋና ጸሎት መጀመሬ ነበር፤ አስደንጋጭ ራእይ አየሁኝ።
ሰማይን የሸፈኑ ነጫጭ መላእክቶች ወደ መሬት እንደ ዝናብ ይወርዱ ነበር። በሦስት የተከፈሉ ምድቦች ናቸው።
• 1ኛው ምድብ፤ በምድር ዙርያ የዓለም ሲሶ የሚያህል ሰው ከሰው መካከል ለይተው ይዘው ወደ ሰማይ ሄዱ። በዚህ ምክንያት ብዙዎች በድንጋጤ ተዋጡ።
• 2ኛው ምድብ፤ የምድር አመጸኞችንና ክፉዎችን እየለዩ መተው ገደሏቸው። ምድር በሬሳ ተሞላች።
• ሶስተኛ ምድብ፤ በእጃቸው የዘይት ቀንድ የያዙ ናቸው፤ በምድሪቱ ዙርያ በብዙዎች ሕፃናቶች፣ ወጣቶች፣ አዛውንቶች፣ ሴቶችና ወንዶች ላይ አፈሰሱ፤ የክብር መጎናጸፊያም አለበሷቸውና ሁሉም በዓለም ሁሉ ተበተኑ፤ ወደ ተመረጠች ወደ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን እንደ እሳት እየተፈነጠሩ በበርና በመስኮቶች ገቡና የቤተክርስቲያን መሠረቶች በኃይል መጽናት ጀመሩ። ያኔ ብዙዎች በኃይል እየተሞሉ በመንፈስ እየሰከሩ ሲያመሰግኑ እያለ አንድ ትልቅ ሽማግሌ ተፈጽሞአልና አሁን ይመጣል ብሎ ሲጮህ አየሁኝ።
"ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።
የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል፤ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፥ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይቀልጣል፥ ምድርም በእርስዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል።
ይህ ሁሉ እንዲህ የሚቀልጥ ከሆነ፥ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኰላችሁ፥ በቅዱስ ኑሮ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንደ ምን ልትሆኑ ይገባችኋል? ስለዚያ ቀን ሰማያት ተቃጥለው ይቀልጣሉ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይፈታል፤
ነገር ግን ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደ ተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን።”
---2ኛ ጴጥሮስ 3:9-13
አሜን አሜን አሜን፥ ማራናታ፥ ጌታ ሆይ ቶሎ ና፥ ናፍቀንሃል።" ---ሐዋርያ በርናባስ ቶማስ።
ኪሩቤል የክብሩ ወንጌል ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።
======= + =======
በቤተክርስቲያኗ የክብሩ ወንጌል በደስታና በጽድቅ ሥራ ማኅበረተኛ መሆን ለምትፈልጉ፤ ለጸሎትና ለቃሉ አብረን እንትጋ። በገንዘባችሁም ጌታን ማገልገል ለምትሹ:-
Cherubim Gospel of Glory International Church (ኪሩቤል የክብሩ ወንጌል ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን):
Commercial Bank of Ethiopia (CBE): 1000035435496 - Swift Code: CBETETAA
Awash Bank: 01352939185901 - Swift Code: AWINETAA
ለወንጌል ጉዞ አገልግሎት:-
AC Name: Bernabas Tomas Daltet (በርናባስ ቶማስ ዳልቴት)
Commercial Bank of Ethiopia (CBE) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
Account Number: 1 0 0 0 2 7 9 4 8 9 4 7 4
ወላጅ አልባ ልጆችን ለመርዳት (To gladly support orphans):-
AC. Name: Bernabas Tomas Daltet
Bank of Abyssinia (BOA) አቢሲኒያ ባንክ
Account Number: 50 58 32 01 - Swift Code: ABYSETAA
ሐዋርያው በርናባስ ቶማስ:-
Ac. Name: Barnabas Tomas Daltet (በርናባስ ቶማስ ዳልቴት)
Birhan Bank (ብርሃን ባንክ): 1000774562091 - Swift Code: BERHETAA
Hibret Bank (ሕብረት ባንክ): 1170410759481015 - Swift Code: UNTDETAA
======= + =======
አድራሻ:- ከጃክሮስ አደባባይ ወደጎሮ በሚወስደው መንገድ የረር አለማየሁ ሕንጻ ፊት ለፊት ሸገር ኮሌጅ አጠገብ።
ለጸሎት +251 911 864 084 | +251 922 363 291
ማራናታ
ጌታ ኢየሱስ ይመጣል።
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ቶሎ ና።

Пікірлер

    Келесі