#ደሃ

መልዕክት ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እስከ ከተማና ወረዳ ተሿሚዎች...
- ሹመት የህዝብ አደራ ነውና የተሰጣችሁን አደራ በታማኝነትና በቅንነት ህዝባችሁን አገልግሉ...
- በተሰጣችሁ ሹመት አትኮፈሱ: አትመፃደቁ: አንዳንዶች ጠባቂ ይመደብልን የሚል ጥያቄ ሁሉ አቅርባችኋል። ሠው ከኑሮው አልፎ አንተን የሚመለከትበት ጊዜ የለውም።
- ህዝብህን በተለይ አቅም የሌላቸው ድሆች መፍትሔን ፍለጋ ሲመጡ በትህትናና በቅንነት ችግሮቻቸውን ተረዷቸው: አታመናጭቋቸው:አትበድሏቸው: የደሃ እንባ ከባድ ነውና!
- ከሌብነት የፀዳ ሁኑ: ልጆቻችሁ የሌባ ልጅ እንዲባሉ አታድርጉ:
- ስለ ሰዎች ወሬ ሲያቀብሏችሁ: ስለሰማችሁት የግለሰብ ወሬ ላይ ተንተርሳችሁ ሠዎችን ለመጥላት አትቸኩሉ: በራሳችሁ መንገድ አጣሩ: ችግር አለበት ስለተባለ ሰው አቅርባችሁ አውሩት: ምናልባት ችግሩ ያለው ወሬ አቀባዩ ጋር ሊሆን ስለሚችል:
- ወጣቱን ፎርማልና ኢንፎማል ግሩፕ ነው እያላችሁ አትፈርጁ: አትነጣጥሉት: ይህች ሀገር ችግር ሲደርስባት ቀድሞ የሚሰዋላት ወጣቱ ነው። ባይሆን ተቀራርባችሁ ልዪነቶችን በውይይት ፍቱ: ውይይት የማይፈታው ችግር የለምና ወጣቱን አንድ አድርጋችሁ ምሩት:
- ስልክ ሲደወልላችሁ አንስታችሁ አውሩ:ቴክስትም መልሱ
- ለሁሉንም ባለሙያ እኩል እይታ ይኑራችሁ
- በተረፈ ከአዲሱ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እስከ ወረዳና ከተማ የህዝብን አደራ ለማገልገል አዳዲስ የተሾማችሁ: ዳግም ህዝባችሁን ለማገልገል እድሉ ለተሰጣችሁ እንዲሁም በማገልገል ላይ ለነበራችሁ በሙሉ መልካም የህዝብ ማገልገል ጊዜ እንዲሆንላችሁ እየተመኘሁ: "ፍርድ ጎደለ: ደሃ ተበደለ" ወሬ የማንሰማበት ጊዜም
ይሁን...ሠላም! የካህናት አባት !!!
የ30 ዓመታት መታሰቢያ
ዘር ተክቶ ማለፍ ከእግዚአብሔር ታድለው፣
ዛሬ በምድር የሉም አርፈዋል ተጠርተው።
የማይቀር ሆኖ እንጂ ማሰብ እንደገና፣
የእኔ አባት በአምላክ ዘንድ አሉ በምስጋና።
ሞት ጉልበት የለውም ይኽንን አውቃለሁ፣
የትንሣኤው ብርሃን ጋርዷቸው አያለሁ።
ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሞት ሽሯል፣
አባቴ ይረፉም ከተድላው ገብተዋል።
ለምን እንደማዝን አውቃለሁ መልስ አለኝ፣
ዕለት ዕለት መሰማት የአባት ቃል ናፈቀኝ።
ደሃ ተበደለ ፍርድ ጎድሏል ብለው፣
ዓይኔ አይቷል ሲረዱት የተገፋውን ሰው።
ፍርድ አዋቂ አባቴ ከዓይን ጠፍተው ዛሬ፣
መመገብ ብርቅ ሆነኝ ከምክራቸው ፍሬ።
ቁጣ ተግሣጽ ትምህርት ደግፎ ያቆመኝ፣
ወልጄ ብከብድም ዛሬም አስፈለገኝ።
የአባቴን ምርቃት እሻለሁ አጥብቄ፣
በረከት በዚያ አለ አውቃለሁ ጠንቅቄ።
እንደ ያዕቆብ ልጆች በአባቴ ፊት ቆሜ፣
መመረቅ አምሮኛል እንዲቀለኝ ሸክሜ።
በዕድሜ በዘመኔ እንደ ስንቅ የያዝኩት፣
የማያልቀው ፍሬ ዛሬም ያልጨረስኩት፣
የአባቴ ምክራቸው አለ ከእኔ ጋራ፣
" ሰው ሲወድህ ፍራ ሰው ሲጠላህ ኩራ "
የሚወደድ ምክር የዘመን ስንቅ ነው፣
ይኽንን አንደበት ዛሬ የት ላግኘው?
እግዚአብሔርን ፈሪ የብዙዎች አባት፣
የመቅደስ አገልጋይ ወልደዋል ካህናት።
ከማልረሳው ነገር ዘወትር ከማስበው፣
የአባቴ ይረፉን የደስታ ዕንባ ነው።
አምስት ልጆቹ ለቅዳሴ ገብተን፣
ምስጋና ስናደርስ መንበሩ ፊት ቆመን፣
ፈንቅሎ እየወጣ አልቆም ብሎ ዕንባቸው፣
ያለቅሱ ነበረ ወደ ፈጣሪያቸው።
የካህናት አባት ካህናት ያፈሩ፣
ዘመኑ ቢረዝምም በአምላክ ከተጠሩ፣
ምንኛ በረካሁ ደስ ባለኝ ነበር፣
በአባቴ ፊት ቆሜ የልቤን ብናገር።
ተራዬን ስዘጋጅ ለማቅረብ ምስጋና፣
አባቴን ነጠቀኝ ሞት ድንገት መጣና።
አይበረክት ሆኖ ደግ ሰው በምድር፣
ከዚህ ድንኳን ዓለም ሄደዋል በክብር።
ጠሪው ክርስቶስ ነው እርሱ እንደወደደ፣
በሰማይ በምድር ሁሉን አደረገ።
በዓለም ላይ ያለውን ይኽንን ፈተና፣
ሳያዩት አለፉ አምላክ ፈቅዷልና።
አትውጣ ተብሎ ሁሉ ከቤት ቀርቶ፣
ሰው ከሰው እንዳይቀርብ ደጃፉ ተዘግቶ፣
በዘር ተከፋፍለን በቋንቋ ተጣልተን፣
ከአንድነት ከፍቅር ልዩነትን መርጠን፣
ዓለም ግራ ገብቶት ስትጨነቅ ምድር፣
ዙሪያዋን ሲከባት መልስ የሌለው ችግር፣
ሰው ወዳድ አክባሪው የእኔ አባት ይረፉ፣
የዓለምን ትርምስምስ ሳያዩ አንቀላፉ።
እምነቴ ሙሉ ነው የለኝም ጥርጥር፣
በማይቀረው ተድላ በትንሣኤው ክብር፣
የታመነ ቃል ነው አባቴን አያለሁ፣
ሁሉ በክርስቶስ እንዲቻል አውቃለሁ።
አባቴ መንገዶት መምጫዬ ነውና
አይርሱኝ በጸሎት በቤቱ እንድጸና
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
መልአከ ገነት ቀሲስ በለጠ ይረፉ
ሚያዝያ 23. 2012. ዓ/ም
በእግዚአብሔር ይዳኛል !!ስለዚህ ደሃ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ ብሎ መፍትሔ ለማበጀት ተፈጥራለሁ። ስለዚህ ወገኖች በተለይ መሪ የሆንን ሰዎች ለተቸገሩት መፍትሔ ላጡት በእግዚአብሔር ቃል ላይ ቆመን ምድራዊ ጥያቄዎቻቸውን መመለስ እውነትን መግለጥ የልባቸውን ጥያቄ መመለስ እንድንችል ፈጣሪ ማስተዋል ይስጠን #ማስተዋል_ይብዛልን ።
" በሰማርያ ተራራ የምትኖሩ፥ ድሆችንም የምትበድሉ፥ ችጋረኞችንም የምታሰጨንቁ፥ ጌቶቻቸውንም። አምጡ እንጠጣ የምትሉ እናንተ የባሳን ላሞች ሆይ፥ ይህን ቃል ስሙ። "እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክ ነኝ !! ህዝቤን አጽናኑ

Пікірлер: 18

  • @yamariyamasfaw8579
    @yamariyamasfaw857918 күн бұрын

    ❤❤❤❤❤❤❤❤❤

  • @Berke-p2h
    @Berke-p2h21 күн бұрын

    ❤💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪✌✌✌🙏🙏🙏🙏🙏

  • @user-xr6zg8ne7i
    @user-xr6zg8ne7i18 күн бұрын

    በትክክክል❤❤❤❤ወድማችን

  • @OusmanMuhammad1311
    @OusmanMuhammad131118 күн бұрын

    ክክክክክ ዘመድኩን ነው ወየ እንድ ሚናገረው ብዬ ለማመን ተቸገርኩ ክክክክክክክ😢😢😢😢😮😮

  • @user-kd1zq9zh8z
    @user-kd1zq9zh8z20 күн бұрын

    እወነትንሐቅንአባሮታል

  • @belayneshwerku-eo9zn
    @belayneshwerku-eo9zn16 күн бұрын

    ለመሆኑ እስክድር ነጋ እንድ አይነት ጭራቅ ነውእንደ ፈጣሬ ስራዉን ይሰጠው

  • @Zeyedegebertsadick
    @Zeyedegebertsadick21 күн бұрын

    ይሕ የሰብአዊ መብት ዓላማ ነው

  • @tesfayedenbel1304
    @tesfayedenbel1304Күн бұрын

    ante koshasha leba

  • @markosalemayehu
    @markosalemayehu19 күн бұрын

    ይቅርታ

  • @gkidangslasie
    @gkidangslasie19 күн бұрын

    እንዲያው የሰው ሂሊና የሌለይ ፊሪሃ እግዚኣቢሄር የሌለህ ሰው የማትለይ ኣረመኔ ተፈጥሮ ለመቀየር የምትመኩር ኣማኝ መሰለህ ሳጥናኢል ሞነርህ ርግጠኛ ያልሆንክ መርዝ ረጭተህ የዘለኣለም እርኩሰ ዘይጋ እንደኣንተ አኣላየሁም የደደቦች ደደብ ሞሰለኒ ሂትለር በ10እጥፍ የምትበልጥ

  • @AlexAddis-jp9tk
    @AlexAddis-jp9tk11 күн бұрын

    አንተ ቡችላ ጎጠኛ ክፍታፍ የሆንክ ነገር።

  • @Crismoses-nd1fq
    @Crismoses-nd1fq12 күн бұрын

    ተበዳ ዘመድኩን አንተ ቡሺቲ እንዳንተ ቦርኮ አለ እንዴ ።

  • @Crismoses-nd1fq

    @Crismoses-nd1fq

    12 күн бұрын

    ድል ለታላቁ እስክንድር

  • @fikretefera6731
    @fikretefera673110 күн бұрын

    አንተ ብሎ መምህር "አወቅሽ አወቅሽ ሲሏት የቄሱ ሚስት መፅሀፍ አጠበች" እንደሚባለው ምነው አንተ እራስህን ከሰው በላይ ነኝ አልክ ! ይህን ቅድ እና ባለጌ አፍህን በልክ አድርገው ማፈሪያ እና ወራዳ ነህ!!!

  • @user-dy3xw9cx1w
    @user-dy3xw9cx1w16 күн бұрын

    አንደአንተ ያ ክፍት አፍ ና ውሸታም አለ? 1

Келесі